መዝሙር 122 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 122:1-9

መዝሙር 122

ኢየሩሳሌም እልል በዪ!

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ።

1“ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ”

ባሉኝ ጊዜ፣ ደስ አለኝ።

2ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እግሮቻችን ከደጅሽ ውስጥ ቆመዋል።

3ኢየሩሳሌም እጅግ እንደ ተጠጋጋች፣

ከተማ ሆና ተሠርታለች።

4ለእስራኤል በተሰጠው ሥርዐት መሠረት፣

የእግዚአብሔርን ስም ለማመስገን፣

የእግዚአብሔር ነገዶች

ወደዚያ ይመጣሉ።

5በዚያም የፍርድ ዙፋኖች የሆኑት፣

የዳዊት ቤት ዙፋኖች ተዘርግተዋል።

6እንዲህ ብላችሁ ለኢየሩሳሌም ሰላም ጸልዩ፤

“የሚወድዱሽ ይለምልሙ፤

7በቅጥርሽ ውስጥ ሰላም ይሁን፤

በምሽግሽም ውስጥ መረጋጋት ይስፈን”።

8ስለ ወንድሞቼና ስለ ባልንጀሮቼ፣

“በውስጥሽ ሰላም ይስፈን” እላለሁ።

9ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት፣

በጎነትሽን እሻለሁ።

Ketab El Hayat

مزمور 122:1-9

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالثَّانِي وَالْعِشْرُونَ

تَرْنِيمَةُ الْمَصَاعِدِ

1فَرِحْتُ بِالْقَائِلِينَ لِي: لِنَذْهَبْ مَعاً إِلَى بَيْتِ الرَّبِّ. 2تَقِفُ أَقْدَامُنَا الآنَ دَاخِلَ أَبْوَابِكِ يَا أُورُشَلِيمُ. 3أُورُشَلِيمُ الْمَبْنِيَّةُ كَمَدِينَةٍ مُتَمَاسِكَةٍ مُتَّحِدَةٍ. 4إِلَيْهَا صَعِدَتِ الأَسْبَاطُ، أَسْبَاطُ الرَّبِّ لِتَرْفَعَ الشُّكْرَ لَهُ بِحَسَبِ أَوَامِرِهِ. 5هُنَاكَ نُصِبَتْ عُرُوشُ الْقَضَاءِ، عُرُوشُ آلِ دَاوُدَ. 6صَلُّوا لأَجْلِ سَلامِ أُورُشَلِيمَ. لِيُفْلِحْ مُحِبُّوكِ وَيَطْمَئِنُّوا. 7لِيَكُنِ السَّلامُ دَاخِلَ أَسْوَارِكِ، وَالأَمَانُ دَاخِلَ قُصُورِكِ. 8مِنْ أَجْلِ إِخْوَتِي وَأَصْحَابِي أَقُولُ: لِيَسُدْ فِيكِ سَلامٌ. 9مِنْ أَجْلِ الرَّبِّ إِلَهِنَا أَلْتَمِسُ لَكِ خَيْراً.