መዝሙር 122 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 122:1-9

መዝሙር 122

ኢየሩሳሌም እልል በዪ!

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ።

1“ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ”

ባሉኝ ጊዜ፣ ደስ አለኝ።

2ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እግሮቻችን ከደጅሽ ውስጥ ቆመዋል።

3ኢየሩሳሌም እጅግ እንደ ተጠጋጋች፣

ከተማ ሆና ተሠርታለች።

4ለእስራኤል በተሰጠው ሥርዐት መሠረት፣

የእግዚአብሔርን ስም ለማመስገን፣

የእግዚአብሔር ነገዶች

ወደዚያ ይመጣሉ።

5በዚያም የፍርድ ዙፋኖች የሆኑት፣

የዳዊት ቤት ዙፋኖች ተዘርግተዋል።

6እንዲህ ብላችሁ ለኢየሩሳሌም ሰላም ጸልዩ፤

“የሚወድዱሽ ይለምልሙ፤

7በቅጥርሽ ውስጥ ሰላም ይሁን፤

በምሽግሽም ውስጥ መረጋጋት ይስፈን”።

8ስለ ወንድሞቼና ስለ ባልንጀሮቼ፣

“በውስጥሽ ሰላም ይስፈን” እላለሁ።

9ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት፣

በጎነትሽን እሻለሁ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 122:1-9

第 122 篇

为耶路撒冷祷告

大卫上圣殿朝圣之诗。

1人们对我说:

“让我们去耶和华的殿吧!”

我感到欢喜。

2耶路撒冷啊,

我们踏进你的城门了。

3耶路撒冷是一座整齐坚固的城。

4以色列各支派,耶和华的子民,

都遵照祂赐的法度去那里称谢祂。

5那里有审判的王座,

就是大卫家的王座。

6要为耶路撒冷的和平祷告,

愿爱这城的人亨通。

7耶路撒冷啊!

愿你城内有平安,

你的宫里有安宁,

8为了我的亲人和朋友,

我要祈求平安临到你。

9为了我们的上帝耶和华的殿,

我要为你求福祉。