መዝሙር 12 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 12:1-8

መዝሙር 12

ከክፉ ዓለም ለመዳን የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በስምንተኛው ቅኝት የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ደግ ሰው የለምና አንተው ድረስልኝ!

ከሰዎችም መካከል አንድ ታማኝ አይገኝም።

2እርስ በርሳቸው ውሸት ይነጋገራሉ፤

በሽንገላ ከንፈርና በሁለት ልብ ይናገራሉ።

3ሸንጋዩን ከንፈር ሁሉ፣

ነገር የምታበዛውንም ምላስ እግዚአብሔር ያጥፋ!

4እነዚህም፣ “በአንደበታችን እንረታለን፤

ከንፈራችን የእኛ ነው፤12፥4 ወይም ከንፈራችን ማረሻ ምላጫችን ነው ጌታችንስ ማነው?”

የሚሉ ናቸው።

5እግዚአብሔር፣ “ስለ ድኾች መከራ፣

ስለ ችግረኞችም ጩኸት፣

አሁን እነሣለሁ፤

በናፈቁትም ሰላም አኖራቸዋለሁ” ይላል።

6የእግዚአብሔር ቃል የጠራ ቃል ነው፤

ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ፣

በምድር ላይ በከውር እንደ ተፈተነ ብር ነው።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ትጠብቀናለህ፤

ከዚህም ትውልድ ለዘላለም ትከልለናለህ።

8በሰዎች ዘንድ ክፋት ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ፣

ዐመፀኞች በየአቅጣጫው በዛቻ ይዞራሉ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 12:1-8

第 12 篇

祈求上帝帮助

大卫的诗,交给乐长。

1耶和华啊,求你救我们!

因为世上的敬虔人不见了,

忠信的人在人间消失了。

2人人谎话连篇,

花言巧语,口是心非。

3愿你铲除一切花言巧语和狂妄自夸的人。

4他们说:“我们必靠舌头制胜,

嘴唇是我们自己的,

谁管得着我们?”

5耶和华说:“我要保护受欺压的困苦人和哀叹的贫穷人,

使他们如愿以偿。”

6耶和华的应许纯全,

就像在炉中炼过七次的银子。

7耶和华啊,你必保护我们,

永远不容恶人侵害我们。

8众人若抑善扬恶,

恶人必横行无忌。