መዝሙር 118 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 118:1-29

መዝሙር 118

ለዳስ በዓል የቀረበ የጕዞ መዝሙር

1እግዚአብሔር ቸር ነውና አመስግኑት፤

ምሕረቱም ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች።

2የእስራኤል ሕዝብ፣ “ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበል።

3የአሮን ቤት፣ “ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበል።

4እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሁሉ፣

“ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበሉ።

5በተጨነቅሁ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤

እግዚአብሔርም መለሰልኝ፤ ከመጠበብም አወጣኝ።

6እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው፤ አልፈራም፤ ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል?

7ይረዳኝ ዘንድ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው፤

የጠላቶቼንም ውድቀት አያለሁ።

8ሰውን መከታ ከማድረግ ይልቅ፣

በእግዚአብሔር መታመን ይሻላል።

9በገዦች ተስፋ ከማድረግ ይልቅ፣

በእግዚአብሔር መታመን ይሻላል።

10ሕዝቦች ሁሉ ከበቡኝ፤

ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።

11መክበቡንስ በየአቅጣጫው ከበቡኝ፤

ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።

12እንደ ንብ መንጋ ከበቡኝ፤

ነገር ግን እንደሚነድድ እሾኽ ከሰሙ፤

በርግጥም በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።

13ተገፍትሬ ልወድቅ ተንገደገድሁ፤

እግዚአብሔር ግን ረዳኝ።

14እግዚአብሔር ብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤

አዳኝ ሆነልኝ።

15በጻድቃን ድንኳን የእልልታና የሆታ ድምፅ፣

እንዲህ እያለ ያስተጋባል፤

የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች፤

16የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ከፍ ከፍ አለች፤

የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች።”

17ተርፌ በሕይወት እኖራለሁ እንጂ አልሞትም፤

የእግዚአብሔርንም ሥራ ገና እናገራለሁ።

18መገሠጹን እግዚአብሔር እጅግ ገሥጾኛል፤

ነገር ግን ለሞት አሳልፎ አልሰጠኝም።

19የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ፤

በዚያ ገብቼ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።

20ይህች የእግዚአብሔር ደጅ ናት፤

ጻድቃን በእርሷ በኩል ይገባሉ።

21ሰምተህ መልሰህልኛልና፣

አዳኝም ሆነህልኛልና አመሰግንሃለሁ።

22ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣

እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ።

23እግዚአብሔር ይህን አደረገ፤

ለዐይናችንም ድንቅ ናት።

24እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤

በእርሷ ሐሤት እናድርግ፤ ደስም ይበለን።

25እግዚአብሔር ሆይ፤ እባክህ አድነን፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እባክህ አሳካልን።

26በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው።

ከእግዚአብሔር ቤት ባረክናችሁ።

27እግዚአብሔር አምላክ ነው፤

ብርሃኑንም በላያችን አበራ፤

እስከ መሠዊያው118፥27 ወይም የክብረ በዓልን መሥዋዕት በገመድ ማሰር ወይም መውሰድ ቀንዶች ድረስ በመውጣት፣

ዝንጣፊ ይዛችሁ በዓሉን ከሚያከብሩት ጋር ተቀላቀሉ።

28አንተ አምላኬ ነህ፤ አመሰግንሃለሁ፤

አንተ አምላኬ ነህ፤ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ።

29ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

ምሕረቱም ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 118:1-29

118

1さあ、主に感謝しましょう。

主はあわれみ深く、その恵みはいつまでも尽きません。

2イスラエルの人々よ、口々に、

「主の恵みは尽きることがありません」と

ほめたたえなさい。

3アロンの家の祭司よ、

「主の恵みはいつまでも尽きません」と歌いなさい。

4主を信じるようになった外国人も、

「主の恵みはいつまでも尽きません」と歌いなさい。

5苦しみの中から祈り求めると、

主は答えて、救い出してくださいました。

6主は私の味方です。

私には、怖いものなどありません。

ただの人間に何の手出しができましょう。

7主がそばにいて助けてくださるので、

私を憎む者どもが勝ち誇ることはありません。

8人をあてにするより、主を信頼したほうがよいのです。

9力ある王にかくまわれるより、

主の保護を受けるほうがよいのです。

10たとえ、世界中の国が攻めて来ても、

私は主のあとについて進軍し、敵を全滅させます。

11敵に包囲され、攻撃をしかけられても、

私は高々と翻る主の旗のもとで、勇気を得て、

彼らをすべて打ち倒します。

12敵ははちのように群がり、

燃え上がる炎のように襲いかかります。

しかし、私は主の旗のもとで彼らを滅ぼします。

13敵は私を亡き者にしようと図り、

あらゆる手を打って攻めてきましたが、

主はいつも助けてくださいました。

14激戦のさなかに、主は私の力となり、

私は主のことを歌いました。

こうして、私は勝利を手にしました。

15-16私たちの勝利の知らせを聞いて、

主を信じ、従う人々の家には、

喜びの歌がわき起こります。

主はめざましい働きをしてくださいました。

17私はいのちを落とすことなく、生き長らえて、

主のなさったことを人々に語り伝えましょう。

18主は私を懲らしめましたが、

死には渡されませんでした。

19神殿の門よ、開きなさい。

私は中に入って、主に感謝します。

20主を信じて従う人が、

この門から入って主の前に出るのです。

21ああ主よ。

祈りに答えて私を救ってくださったことを、

心の底から感謝します。

22大工の捨てた石が、

今では一番大切な土台石になりました。

23これこそ主のなさることで、

人の思いをはるかに越えています。

24今日こそ、主がお造りになった日です。

さあ、この日をぞんぶんに楽しみましょう。

25ああ主よ、どうかお助けください。お救いください。

私たちがすることを、すべて成功させてください。

26主がまもなく遣わしてくださる方に、

祝福がありますように。

私たちは神殿であなたがたを祝福します。

27-28主は私たちの光です。

私はいけにえを祭壇にささげます。

私は主に感謝し、賛美の声を上げます。

29感謝の祈りをささげましょう。

主はあわれみ深く、

その恵みはいつまでも尽きないからです。