መዝሙር 116 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 116:1-19

መዝሙር 116

ምስጋና

1የልመናዬን ድምፅ ሰምቷልና፣

እግዚአብሔርን ወደድሁት።

2ጆሮውን ወደ እኔ አዘንብሏልና፣

በሕይወት ዘመኔ ሁሉ ወደ እርሱ እጣራለሁ።

3የሞት ወጥመድ ያዘኝ፤

የሲኦልም116፥3 ዕብራይስጡ መቃብር ይላል። ጣር አገኘኝ፤

ጭንቅና ሐዘን አሸነፈኝ።

4እኔም የእግዚአብሔርን ስም ጠራሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ነፍሴን ታድናት ዘንድ እለምንሃለሁ” አልሁ።

5እግዚአብሔር ቸርና ጻድቅ ነው፤

አምላካችን መሓሪ ነው።

6እግዚአብሔር ገሮችን ይጠብቃል፤

እጅግ ተቸግሬ ሳለሁ አዳነኝ።

7ነፍሴ ሆይ፤ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሺ፤

እግዚአብሔር መልካም አድርጎልሻልና፤

8አንተ ነፍሴን ከሞት፣

ዐይኔን ከእንባ፣

እግሮቼን ከመሰናከል አድነሃልና።

9እኔም በሕያዋን ምድር፣

በእግዚአብሔር ፊት እመላለሳለሁ።

10“እጅግ ተጨንቄአለሁ” ባልሁበት ጊዜ እንኳ፣116፥10 ወይም ያኔ እንኳን

እምነቴን ጠብቄአለሁ።

11ግራ በተጋባሁ ጊዜ፣

“ሰው ሁሉ ሐሰተኛ ነው” አልሁ።

12ስለ ዋለልኝ ውለታ ሁሉ፣

ለእግዚአብሔር ምን ልክፈለው?

13የመዳንን ጽዋ አነሣለሁ፤

የእግዚአብሔርንም ስም እጠራለሁ።

14በሕዝቡ ሁሉ ፊት፣

ስእለቴን ለእግዚአብሔር እፈጽማለሁ።

15የቅዱሳኑ ሞት፣

በእግዚአብሔር ፊት የተከበረ ነው።

16እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔ በእውነት ባሪያህ ነኝ፤

እኔ የሴት ባሪያህ116፥16 ታማኝ አገልጋይህ ወይም ታማኝ ልጅህ ልጅ፣ ባሪያህ ነኝ፤

ከእስራቴም ፈታኸኝ።

17ለአንተ የምስጋና መሥዋዕት አቀርባለሁ፤

የእግዚአብሔርንም ስም እጠራለሁ።

18በሕዝቡ ሁሉ ፊት፣

ስእለቴን ለእግዚአብሔር እፈጽማለሁ፤

19ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ይህን በመካከልሽ፣

በእግዚአብሔር ቤት አደባባይ አደርጋለሁ።

ሃሌ ሉያ።116፥19 አንዳንዶች እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 116:1-19

第 116 篇

感謝拯救之恩

1我愛耶和華,

因為祂垂聽了我的呼求和禱告。

2因為祂垂聽我的祈求,

我一生都要向祂禱告。

3死亡的繩索纏繞我,

陰間的恐怖籠罩我,

我被困苦和憂愁淹沒。

4於是,我求告耶和華,

說:「耶和華啊,求你拯救我。」

5耶和華仁慈、公義,

我們的上帝充滿憐憫。

6耶和華保護心地單純的人,

危難之時祂救了我。

7我的心啊,再次安寧吧,

因為耶和華恩待你。

8祂救我的性命脫離死亡,

止住我眼中的淚水,

使我雙腳免於滑倒。

9我要在世上事奉耶和華。

10我相信,所以才說:

「我受盡了痛苦。」

11我曾驚恐地說:

「人人都說謊。」

12我拿什麼報答耶和華賜給我的一切恩惠呢?

13我要為耶和華的拯救之恩而舉杯稱頌祂的名。

14我要在耶和華的子民面前還我向祂許的願。

15耶和華的眼目顧惜祂聖民的死亡。

16耶和華啊!我是你的僕人,

是你的僕人,是你婢女的兒子。

你除去了我的鎖鏈。

17我要向你獻上感恩祭,

呼求你的名。

18-19我要在耶路撒冷

在耶和華的殿中,

在耶和華的子民面前還我向祂許的願。

你們要讚美耶和華!