መዝሙር 114 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 114:1-8

መዝሙር 114

ለፋሲካ የቀረበ ውዳሴ

1እስራኤል ከግብፅ ወጥቶ ሲሄድ፣

የያዕቆብም ቤት ቋንቋው ልዩ ከሆነ ሕዝብ ተለይቶ ሲወጣ፣

2ይሁዳ የእግዚአብሔር መቅደስ፣

እስራኤልም ግዛቱ ሆነ።

3ባሕር አየች፤ ሸሸችም፤

ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ።

4ተራሮች እንደ አውራ በግ፣

ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ዘለሉ።

5አንቺ ባሕር፤ የሸሸሽው አንቺም ዮርዳኖስ ያፈገፈግሽው ለምንድን ነው?

6እናንተ ተራሮች እንደ አውራ በግ፣

ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ለምን ዘለላችሁ?

7ምድር ሆይ፤ በጌታ ፊት፣

በያዕቆብ አምላክ ፊት ተንቀጥቀጪ፤

8እርሱ ዐለቱን ወደ ኵሬ፣

ቋጥኙንም ወደ ውሃ ምንጭ ለወጠ።

New International Version – UK

Psalms 114:1-8

Psalm 114

1When Israel came out of Egypt,

Jacob from a people of foreign tongue,

2Judah became God’s sanctuary,

Israel his dominion.

3The sea looked and fled,

the Jordan turned back;

4the mountains leaped like rams,

the hills like lambs.

5Why was it, sea, that you fled?

Why, Jordan, did you turn back?

6Why, mountains, did you leap like rams,

you hills, like lambs?

7Tremble, earth, at the presence of the Lord,

at the presence of the God of Jacob,

8who turned the rock into a pool,

the hard rock into springs of water.