መዝሙር 114 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 114:1-8

መዝሙር 114

ለፋሲካ የቀረበ ውዳሴ

1እስራኤል ከግብፅ ወጥቶ ሲሄድ፣

የያዕቆብም ቤት ቋንቋው ልዩ ከሆነ ሕዝብ ተለይቶ ሲወጣ፣

2ይሁዳ የእግዚአብሔር መቅደስ፣

እስራኤልም ግዛቱ ሆነ።

3ባሕር አየች፤ ሸሸችም፤

ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ።

4ተራሮች እንደ አውራ በግ፣

ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ዘለሉ።

5አንቺ ባሕር፤ የሸሸሽው አንቺም ዮርዳኖስ ያፈገፈግሽው ለምንድን ነው?

6እናንተ ተራሮች እንደ አውራ በግ፣

ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ለምን ዘለላችሁ?

7ምድር ሆይ፤ በጌታ ፊት፣

በያዕቆብ አምላክ ፊት ተንቀጥቀጪ፤

8እርሱ ዐለቱን ወደ ኵሬ፣

ቋጥኙንም ወደ ውሃ ምንጭ ለወጠ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 114:1-8

114

1昔、イスラエルの民は、ことばの通じない異国の地、

エジプトから逃げ出して来ました。

2その時、ユダとイスラエルの地は、

神の新しい住まいとなり、王国となったのです。

3紅海は、神の民の近づく足音にあわてて二つに分かれ、

ヨルダン川は、歩いて渡れる道を作りました。

4山は雄羊のように、丘は子羊のように跳びはねました。

5なぜ、紅海は二つに分かれたのですか。

どうして、ヨルダン川の水が逆流したのですか。

6なぜ、山は雄羊のように跳びはね、

丘は子羊のように躍ったのですか。

7大地よ、主の前におののきなさい。

8神は、堅い岩から、

ほとばしる泉のように水を出された方だからです。