መዝሙር 113 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 113:1-9

መዝሙር 113

ለታላቁና ለመሓሪው ጌታ ምስጋና

1ሃሌ ሉያ።113፥1 እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ሲሆን፣ በ9 ላይም ይገኛል።

የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

የእግዚአብሔርን ስም አወድሱ።

2ከአሁን እስከ ዘላለም፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

3ከፀሓይ መውጫ እስከ መግቢያው ድረስ፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

4እግዚአብሔር ከሕዝቦች ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፤

ክብሩም ከሰማያት በላይ ነው።

5እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር

በላይ በዙፋኑ የተቀመጠ ማን ነው?

6በሰማይና በምድር ያሉትንስ ለማየት፣

ራሱን ወደ ታች ዝቅ የሚያደርግ ማን ነው?

7ድኻውን ከትቢያ ያነሣል፤

ችግረኛውን ከዐመድ ከፍ ከፍ ያደርጋል፤

8ከመኳንንትም እኩል ስፍራ ይሰጠዋል፤

ከሕዝቡም ሹማምት ጋር ያስቀምጠዋል።

9መካኒቱን ሴት በቤት ያኖራታል፤

ደስተኛም የልጆች እናት ያደርጋታል።

ሃሌ ሉያ።

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 113:1-9

สดุดี 113

1จงสรรเสริญองค์พระผู้เป็นเจ้า113:1 ภาษาฮีบรูว่าฮาเลลูยาเช่นเดียวกับข้อ 9

จงสรรเสริญเถิด บรรดาผู้รับใช้ขององค์พระผู้เป็นเจ้า

จงสรรเสริญพระนามของพระยาห์เวห์

2ขอให้พระนามของพระยาห์เวห์เป็นที่สรรเสริญ

ตั้งแต่บัดนี้และสืบไปนิรันดร

3ตั้งแต่ที่ดวงอาทิตย์ขึ้น จนถึงที่ดวงอาทิตย์ตก

พระนามของพระยาห์เวห์จะเป็นที่สรรเสริญ

4องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเป็นที่ยกย่องเทิดทูนเหนือมวลประชาชาติ

พระเกียรติสิริของพระองค์สูงส่งกว่าฟ้าสวรรค์

5ผู้ใดจะเสมอเหมือนพระยาห์เวห์พระเจ้าของเรา?

ผู้ประทับบนบัลลังก์เบื้องสูง

6ผู้ทรงโน้มพระองค์ลงมา

ทอดพระเนตรฟ้าสวรรค์และแผ่นดินโลก

7พระองค์ทรงยกคนยากจนขึ้นจากฝุ่นธุลี

ทรงยกคนขัดสนขึ้นจากกองขี้เถ้า

8พระองค์ทรงให้เขานั่งร่วมกับเจ้านาย

กับเจ้านายแห่งชนชาติของเขา

9พระองค์ประทานเหย้าเรือนแก่ผู้หญิงที่เป็นหมัน

เพื่อเธอจะเป็นมารดาผู้มีสุขของลูกๆ

จงสรรเสริญองค์พระผู้เป็นเจ้า