መዝሙር 113 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 113:1-9

መዝሙር 113

ለታላቁና ለመሓሪው ጌታ ምስጋና

1ሃሌ ሉያ።113፥1 እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ሲሆን፣ በ9 ላይም ይገኛል።

የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

የእግዚአብሔርን ስም አወድሱ።

2ከአሁን እስከ ዘላለም፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

3ከፀሓይ መውጫ እስከ መግቢያው ድረስ፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

4እግዚአብሔር ከሕዝቦች ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፤

ክብሩም ከሰማያት በላይ ነው።

5እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር

በላይ በዙፋኑ የተቀመጠ ማን ነው?

6በሰማይና በምድር ያሉትንስ ለማየት፣

ራሱን ወደ ታች ዝቅ የሚያደርግ ማን ነው?

7ድኻውን ከትቢያ ያነሣል፤

ችግረኛውን ከዐመድ ከፍ ከፍ ያደርጋል፤

8ከመኳንንትም እኩል ስፍራ ይሰጠዋል፤

ከሕዝቡም ሹማምት ጋር ያስቀምጠዋል።

9መካኒቱን ሴት በቤት ያኖራታል፤

ደስተኛም የልጆች እናት ያደርጋታል።

ሃሌ ሉያ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 113:1-9

第 113 篇

赞美上帝的美善

1你们要赞美耶和华!

耶和华的仆人啊,

你们要赞美,赞美耶和华。

2愿耶和华的名受称颂,

从现在直到永远!

3从日出之地到日落之处,

普世都应当赞美耶和华。

4耶和华高居万国之上,

祂的荣耀高过诸天。

5谁能与我们的上帝耶和华相比?

祂坐在至高之处,

6俯视诸天和大地。

7祂从灰尘中提拔贫穷人,

从粪堆中擢升困苦人,

8使他们与王子同坐,

与本国的王子同坐。

9祂赐给不育的妇人儿女,

使她们成为快乐的母亲。

你们要赞美耶和华!