መዝሙር 110 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 110:1-7

መዝሙር 110

መሲሑ ንጉሥና ካህን

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ጌታዬን፣

“ጠላቶችህን ለእግርህ መርገጫ፣

እስከማደርግልህ ድረስ፣

በቀኜ ተቀመጥ” አለው።

2እግዚአብሔር ብርቱ በትርህን ከጽዮን ወደ ውጭ ይሰድዳል፤

አንተም በጠላቶችህ መካከል ሆነህ ትገዛለህ።

3ለጦርነት በምትወጣበት ቀን፣

ሰራዊትህ በገዛ ፈቃዱ በጐንህ ይቆማል፤

ከንጋት ማሕፀን፣

በቅዱስ ግርማ ደምቀህ፣

የጕልማሳነትህን ልምላሜ110፥3 ወይም ጐልማሶችህ እንደ ንጋት ወዳንተ ይመጣሉ ማለት ነው። እንደ ጠል ትቀበላለህ።

4“እንደ መልከጼዴቅ ሥርዐት፤

አንተ ለዘላለም ካህን ነህ” ብሎ፣

እግዚአብሔር ምሏል፤

እርሱ ሐሳቡን አይለውጥም።

5ጌታ በቀኝህ ነው፤

በቍጣውም ቀን ነገሥታትን ያደቅቃቸዋል።

6በሕዝቦች መካከል ይፈርዳል፤

በየአገሩ ያሉትንም ራሶች ከስክሶ ሬሳ በሬሳ ያደርጋቸዋል።

7መንገድ110፥7 ወይም ሥልጣን ለመስጠት ኀይል ያለው ሥልጣን ላይ ያስቀምጠዋል ዳር ካለች ፈሳሽ ውሃ ይጠጣል፤

ስለዚህ ራሱን ቀና ያደርጋል።

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 110:1-7

สดุดี 110

(บทสดุดีของดาวิด)

1องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับเจ้านาย110:1 หรือองค์พระผู้เป็นเจ้าของข้าพเจ้าว่า

“จงนั่งที่ขวามือของเรา

จนกว่าเราจะทำให้ศัตรูของเจ้า

เป็นแท่นวางเท้าของเจ้า”

2องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงใช้คทาทรงฤทธิ์ของท่าน

แผ่อำนาจออกไปจากศิโยน

ท่านจะปกครองในหมู่อริราชศัตรู

3ในวันที่ท่านออกศึก

กองทหารของท่านจะเต็มใจอาสาสู้รบ

ตั้งแนวรบด้วยพระบารมีศักดิ์สิทธิ์

ท่านจะได้รับหยาดน้ำค้างแห่งวัยฉกรรจ์110:3 หรือคนหนุ่มของท่านจะออกมาหาท่านเหมือนน้ำค้าง

จากครรภ์แห่งรุ่งอรุณ

4องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ทรงปฏิญาณแล้ว

และจะไม่ทรงเปลี่ยนพระทัยคือ

“เจ้าเป็นปุโรหิตชั่วนิรันดร์

ตามแบบของเมลคีเซเดค”

5องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงประทับเบื้องขวาของท่าน

พระองค์จะทรงบดขยี้กษัตริย์ทั้งหลายในวันแห่งพระพิโรธของพระองค์

6พระองค์จะทรงพิพากษานานาประชาชาติ ทำให้ผู้คนล้มตายเกลื่อนกลาด

จะทรงบดขยี้ผู้นำทั่วโลก

7ท่านจะดื่มน้ำจากลำธารริมทาง110:7 หรือพระองค์ผู้ประทานการสืบทอดอำนาจจะตั้งท่านไว้ให้ปกครอง

ฉะนั้นท่านจะผงาดเกรียงไกร