መዝሙር 110 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 110:1-7

መዝሙር 110

መሲሑ ንጉሥና ካህን

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ጌታዬን፣

“ጠላቶችህን ለእግርህ መርገጫ፣

እስከማደርግልህ ድረስ፣

በቀኜ ተቀመጥ” አለው።

2እግዚአብሔር ብርቱ በትርህን ከጽዮን ወደ ውጭ ይሰድዳል፤

አንተም በጠላቶችህ መካከል ሆነህ ትገዛለህ።

3ለጦርነት በምትወጣበት ቀን፣

ሰራዊትህ በገዛ ፈቃዱ በጐንህ ይቆማል፤

ከንጋት ማሕፀን፣

በቅዱስ ግርማ ደምቀህ፣

የጕልማሳነትህን ልምላሜ110፥3 ወይም ጐልማሶችህ እንደ ንጋት ወዳንተ ይመጣሉ ማለት ነው። እንደ ጠል ትቀበላለህ።

4“እንደ መልከጼዴቅ ሥርዐት፤

አንተ ለዘላለም ካህን ነህ” ብሎ፣

እግዚአብሔር ምሏል፤

እርሱ ሐሳቡን አይለውጥም።

5ጌታ በቀኝህ ነው፤

በቍጣውም ቀን ነገሥታትን ያደቅቃቸዋል።

6በሕዝቦች መካከል ይፈርዳል፤

በየአገሩ ያሉትንም ራሶች ከስክሶ ሬሳ በሬሳ ያደርጋቸዋል።

7መንገድ110፥7 ወይም ሥልጣን ለመስጠት ኀይል ያለው ሥልጣን ላይ ያስቀምጠዋል ዳር ካለች ፈሳሽ ውሃ ይጠጣል፤

ስለዚህ ራሱን ቀና ያደርጋል።

King James Version

Psalms 110:1-7

A Psalm of David.

1The LORD said unto my Lord, Sit thou at my right hand, until I make thine enemies thy footstool.

2The LORD shall send the rod of thy strength out of Zion: rule thou in the midst of thine enemies.

3Thy people shall be willing in the day of thy power, in the beauties of holiness from the womb of the morning: thou hast the dew of thy youth.110.3 from…: or, more than the womb of the morning: thou shalt have, etc

4The LORD hath sworn, and will not repent, Thou art a priest for ever after the order of Melchizedek.

5The Lord at thy right hand shall strike through kings in the day of his wrath.

6He shall judge among the heathen, he shall fill the places with the dead bodies; he shall wound the heads over many countries.110.6 many: or, great

7He shall drink of the brook in the way: therefore shall he lift up the head.