መዝሙር 105 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 105:1-45

መዝሙር 105

የእስራኤል ድንቅ ታሪክ

105፥1-15 ተጓ ምብ – 1ዜና 16፥8-22

1እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ስሙንም ጥሩ፤

ሥራውንም በሕዝቦች መካከል ግለጡ።

2ተቀኙለት፤ ዘምሩለት፤

ድንቅ ሥራዎቹንም ሁሉ ተናገሩ።

3በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤

እግዚአብሔርን የሚሹት ልባቸው ደስ ይበለው።

4እግዚአብሔርንና ብርታቱን ፈልጉ፤

ፊቱንም ዘወትር ፈልጉ።

5ያደረጋቸውን ድንቅ ሥራዎች፣

ታምራቱንና ከአፉ የወጣውን ፍርድ አስቡ፤

6እናንተ የአገልጋዩ የአብርሃም ዘሮች፣

ለራሱም የመረጣችሁ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፤ አስታውሱ።

7እርሱ እግዚአብሔር አምላካችን ነው፤

ፍርዱም በምድር ሁሉ ላይ ነው።

8ኪዳኑን ለዘላለም፣

ያዘዘውንም ቃል እስከ ሺሕ ትውልድ ያስታውሳል።

9ከአብርሃም ጋር ያደረገውን ኪዳን፣

ለይስሐቅም በመሐላ የተሰጠውን ተስፋ አይረሳም።

10ይህንም ለያዕቆብ ሥርዐት አድርጎ፣

ለእስራኤልም የዘላለም ኪዳን አድርጎ አጸናለት፤

11እንዲህም አለ፤ “የርስትህ ድርሻ አድርጌ፣

የከነዓንን ምድር እሰጥሃለሁ።”

12በቍጥር አነስተኞች ሆነው ሳሉ፣

እጅግ ጥቂትና ባይተዋሮች ሳሉ፣

13ከሕዝብ ወደ ሕዝብ ሲንከራተቱ፣

ከአንዱ መንግሥት ወደ ሌላው ሲቅበዘበዙ፣

14ማንም ግፍ እንዲፈጽምባቸው አልፈቀደም፤

ስለ እነርሱም ነገሥታትን እንዲህ ሲል ገሠጸ፤

15“የቀባኋቸውን አትንኩ፤

በነቢያቴም ላይ ክፉ አታድርጉ።”

16በምድሪቱ ላይ ራብን ጠራ፤

የምግብንም አቅርቦት ሁሉ አቋረጠ፤

17በባርነት የተሸጠውን ሰው፣

ዮሴፍን ከእነርሱ አስቀድሞ ላከ።

18እግሮቹ በእግር ብረት ተላላጡ፤

በዐንገቱም የብረት ማነቆ ገባ።

19የተናገረው ቃል እስኪፈጸምለት፣

የእግዚአብሔር ቃል ፈተነው።

20ንጉሥ ልኮ አስፈታው፤

የሕዝቦችም ገዥ ነጻ አወጣው።

21የቤቱ ጌታ፣

የንብረቱም ሁሉ አስተዳዳሪ አደረገው፤

22ይኸውም ሹማምቱን በራሱ መንገድ ይመራ ዘንድ፣

ታላላቆቹንም ጥበብ ያስተምር ዘንድ ነበር።

23እስራኤል ወደ ግብፅ ገባ፤

ያዕቆብ በካም ምድር መጻተኛ ሆነ።

24እግዚአብሔር ሕዝቡን እጅግ አበዛ፤

ከጠላቶቻቸውም ይልቅ አበረታቸው፤

25ሕዝቡን እንዲጠሉ፣

በባሪያዎቹም ላይ እንዲያሤሩ ልባቸውን ለወጠ።

26ባሪያውን ሙሴን፣

የመረጠውንም አሮንን ላከ።

27እነርሱም ታምራታዊ ምልክቶችን በመካከላቸው፣

ድንቅ ነገሮቹንም በካም ምድር አደረጉ።

28ጨለማን ልኮ ምድሪቱን ጽልመት አለበሰ፤

እነርሱም በቃሉ ላይ ማመፅን ተዉ።

29ውሃቸውን ወደ ደም ለወጠ፤

ዓሦቻቸውንም ፈጀ።

30ምድራቸውም፣ የነገሥታታቸው እልፍኝ ሳይቀር፣

ጓጕንቸር ተርመሰመሰባቸው።

31እርሱ በተናገረ ጊዜ የዝንብ መንጋ መጣ፤

ትንኞችም ምድራቸውን ወረሩ።

32ዝናባቸውን በረዶ አደረገው፤

ምድራቸውም ሁሉ መብረቅ አወረደ።

33ወይናቸውንና በለሳቸውን መታ፤

የአገራቸውንም ዛፍ ከተከተ።

34እርሱ በተናገረ ጊዜ አንበጣ መጣ፤

ስፍር ቍጥር የሌለውም ኵብኵባ ከተፍ አለ፤

35የምድሪቱንም ዕፀዋት ሁሉ በላ፤

የመሬታቸውንም ፍሬ ሙጥጥ አደረገ፤

36ደግሞም በአገራቸው ያለውን በኵር ሁሉ፣

የኀይላቸውንም ሁሉ በኵራት መታ።

37የእስራኤልንም ሕዝብ ብርና ወርቅ ጭኖ እንዲወጣ አደረገ፤

ከነገዶቻቸውም አንድም አልተደናቀፈም።

38እጅግ ፈርተዋቸው ነበርና፣

ወጥተው ሲሄዱ ግብፅ ደስ አላት።

39ደመናን እንደ መጋረጃ ዘረጋላቸው፤

እሳትም በሌሊት አበራላቸው።

40በለመኑትም ጊዜ፣ ድርጭት አመጣላቸው፤

የሰማይንም እንጀራ አጠገባቸው።

41ዐለቱን ሰነጠቀ፤ ውሃም ተንዶለደለ፤

እንደ ወንዝም በበረሓ ፈሰሰ።

42ለባሪያው ለአብርሃም የሰጠውን፣

ቅዱስ የተስፋ ቃሉን አስቧልና።

43ሕዝቡን በደስታ፣

ምርጦቹንም በእልልታ አወጣቸው።

44የሌሎችን ሕዝቦች ምድር ሰጣቸው፤

የእነዚህንም የድካም ፍሬ ወረሱ፤

45ይህም ሥርዐቱን ይጠብቁ ዘንድ፣

ሕጉንም ይፈጽሙ ዘንድ ነው።

ሃሌ ሉያ።105፥45 እግዚአብሔር ይመስገን የሚሉ ትርጕሞች አሉ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 105:1-45

第 105 篇

上帝和祂的子民

(平行經文:歷代志上16·8-22

1你們要稱謝耶和華,呼求祂的名,

在列邦傳揚祂的作為。

2要歌頌、讚美祂,

述說祂一切奇妙的作為。

3要以祂的聖名為榮,

願尋求耶和華的人都歡欣。

4要尋求耶和華和祂的能力,

時常來到祂面前。

5-6祂僕人亞伯拉罕的後裔,

祂所揀選的雅各的子孫啊,

要記住祂所行的神蹟奇事和祂口中的判詞。

7祂是我們的上帝耶和華,

祂在普天下施行審判。

8祂永遠記得祂的約,

歷經千代也不忘祂的應許,

9就是祂與亞伯拉罕所立的約,

以撒所起的誓。

10祂把這約定為律例賜給雅各

定為永遠的約賜給以色列

11祂說:「我必把迦南賜給你,

作為你的產業。」

12那時他們人丁稀少,

在當地寄居。

13他們在異國他鄉流離飄零。

14耶和華不容人壓迫他們,

還為他們的緣故責備君王,

15說:「不可難為我膏立的人,

也不可傷害我的先知。」

16祂在那裡降下饑荒,

斷絕一切食物的供應。

17祂派一個人率先前往,

這人就是被賣為奴隸的約瑟

18他被戴上腳鐐,套上枷鎖,

19直到後來他的預言應驗,

耶和華的話試煉了他。

20埃及王下令釋放他,

百姓的首領給他自由,

21派他執掌朝政,

管理國中的一切,

22有權柄管束王的大臣,

將智慧傳授王的長老。

23以色列來到埃及

寄居在地。

24耶和華使祂的子民生養眾多,

比他們的仇敵還要強盛。

25祂使仇敵憎恨他們,

用詭計虐待他們。

26祂派遣祂的僕人摩西和祂揀選的亞倫

27埃及行神蹟,

地行奇事。

28祂降下黑暗,使黑暗籠罩那裡;

他們沒有違背祂的話。

29祂使埃及的水變成血,

魚都死去;

30又使國中到處是青蛙,

王宮禁院也不能倖免。

31祂一發命令,

蒼蠅蜂擁而至,蝨子遍滿全境。

32祂使雨變成冰雹,

遍地電光閃閃。

33祂擊倒他們的葡萄樹和無花果樹,

摧毀他們境內的樹木。

34祂一發聲,

就飛來無數蝗蟲和螞蚱,

35吃盡他們土地上的植物,

吃盡他們田間的出產。

36祂又擊殺他們境內所有的長子,

就是他們年輕力壯時生的長子。

37祂帶領以色列人攜金帶銀地離開埃及

各支派中無人畏縮。

38埃及人懼怕他們,

樂見他們離去。

39祂鋪展雲彩為他們遮蔭,

晚上用火給他們照明。

40他們祈求,

祂就賜下鵪鶉,降下天糧,

叫他們飽足。

41祂使磐石裂開、湧出水來,

在乾旱之地奔流成河。

42因為祂沒有忘記祂賜給僕人亞伯拉罕的神聖應許。

43祂帶領自己的子民歡然離去,

祂所揀選的百姓歡唱著前行。

44祂把列國的土地賜給他們,

使他們獲得別人的勞動成果。

45祂這樣做是要使他們持守祂的命令,

遵行祂的律法。

你們要讚美耶和華!