መክብብ 5 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መክብብ 5:1-20

እግዚአብሔርን ፍራ

1ወደ እግዚአብሔር ቤት ስትሄድ እግርህን ጠብቅ። ለመስማት መቅረብ የሰነፎችን መሥዋዕት ከማቅረብ ይበልጣል፤ እነርሱ ክፉ እንደሚሠሩ አያውቁምና።

2በአፍህ አትፍጠን፤

በእግዚአብሔርም ፊት ማንኛውንም ነገር ለመናገር፣

በልብህ አትቸኵል፤

እግዚአብሔር በሰማይ፣

አንተ ደግሞ በምድር ነህ፤

ስለዚህ ቃልህ ጥቂት ይሁን።

3በሥራ ብዛት ሕልም እንደሚታይ፣

ብዙ ቃል ባለበትም የሞኝ ንግግር ይገለጣል።

4ለእግዚአብሔር ስእለትን በተሳልህ ጊዜ ለመፈጸም አትዘግይ፤ በሰነፎች ደስ አይለውምና፤ ስእለትህን ፈጽም። 5ስእለት ተስሎ ካለመፈጸም፣ አለመሳል ይሻላል። 6አንደበትህ ወደ ኀጢአት እንዲመራህ አትፍቀድ፤ ለቤተ መቅደስ መልእክተኛም፣ “የተሳልሁት በስሕተት ነበር” አትበል። እግዚአብሔር በተናገርኸው ተቈጥቶ የእጅህን ሥራ ለምን ያጥፋ? 7ብዙ ሕልምና ብዙ ቃል ከንቱ ነው፤ ስለዚህ እግዚአብሔርን ፍራ።

ባለጠግነት ከንቱ ነው

8በአገር ውስጥ ድኻ ተጨቍኖ፣ ፍትሕ ተጓድሎ፣ መብትም ተረግጦ ብታይ፣ እንደነዚህ ባሉ ነገሮች አትደነቅ፤ ምክንያቱም አንዱን አለቃ የበላዩ ይመለከተዋል፤ በእነዚህ በሁለቱም ላይ ሌሎች ከፍ ያሉ አሉ። 9ከምድሩ የሚገኘው ትርፍ ለሁሉም ነው፤ ንጉሡም ራሱ የሚጠቀመው ከዕርሻ ነው።

10ገንዘብን የሚወድድ፣ ገንዘብ አይበቃውም፤

ብልጽግናም የሚወድድ፣ በትርፉ አይረካም፤

ይህም ከንቱ ነው።

11ሀብት በበዛ ቍጥር፣

ተጠቃሚውም ይበዛል፤

በዐይኑ ብቻ ከማየት በቀር

ታዲያ፣ ለባለቤቱ ምን ይጠቅመዋል?

12ጥቂትም ይሁን ብዙ ቢበላ፣

የሠራተኛ እንቅልፍ ጣፋጭ ነው፤

የሀብታም ሰው ብልጽግና ግን

እንቅልፍ ይነሣዋል።

13ከፀሓይ በታች የሚያሳዝን ክፉ ነገር አየሁ፦

ይህም ለባለቤቱ ጕዳት የተከማቸ ሀብት፣

14ወይም በአንድ መጥፎ አጋጣሚ የጠፋ ብልጽግና ነው፤

ልጅ ሲወልድም፣

ለእርሱ የሚያስቀርለት ምንም ነገር አይኖርም።

15ሰው ከእናቱ ማሕፀን ዕራቍቱን ይወለዳል፤

እንደ መጣው እንዲሁ ይመለሳል።

ከለፋበትም ነገር፣

አንድም እንኳ በእጁ ይዞ ሊሄድ አይችልም።

16ይህ ደግሞ እጅግ ክፉ ነገር ነው፤

ሰው እንደ መጣ እንዲሁ ይሄዳል፤

የሚደክመው ለነፋስ ስለሆነ፣

ትርፉ ምንድን ነው?

17በብዙ ጭንቀት፣ መከራና ብስጭት፣

ዘመኑን ሁሉ በጨለማ ውስጥ ይበላል።

18የሰው ዕጣው ይህ ስለሆነ፣ እግዚአብሔር በሰጠው በጥቂት ዘመኑ ከፀሓይ በታች በሚደክምበት ነገር ርካታን ያገኝ ዘንድ፣ መብላቱና መጠጣቱም መልካምና ተገቢ መሆኑን ተገነዘብሁ። 19እግዚአብሔር ለሰው ባለጠግነትና ሀብት መስጠቱ፣ እንዲደሰትበትም ማስቻሉ፣ ዕጣውን እንዲቀበልና በሥራውም እንዲደሰት ማድረጉ፣ ይህ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው። 20እግዚአብሔር የልብ ደስታ ስለሚሰጠውም በሕይወቱ ዘመን ያሉትን ቀናት እምብዛም አያስባቸውም።

Japanese Contemporary Bible

伝道者の書 5:1-20

5

神への誓いを果たしなさい

1-3神殿に入るときは、耳をすまして、口は堅くつぐみなさい。神に軽はずみな約束をするのは罪です。それがわからないほど愚かになってはいけません。神は天におられ、私たちは地にいるのですから、ことば数はできるだけ少なくすべきです。

仕事が多いと悪夢にうなされ、

口数が多いと愚かになる。

4神に、何かをすると誓いを立てたときは、すぐに実行しなさい。神は、愚かな人間を喜ぶことがないからです。神との約束は、どんなことがあっても果たしなさい。 5何かをすると言いながらしないより、初めから口にしないほうがずっと良いのです。 6-7約束を果たさないなら、口で罪を犯すことになります。神の使者に、「誓いを立てたのは間違いでした」などと弁解してはいけません。それを聞いて神は腹を立て、あなたの繁栄を奪い去るかもしれないからです。

夢ばかり見ていて実行しないのは愚かで、

むなしいことばが多いと、

滅びを招きます。

そんなことをしないで、神を恐れなさい。

富はむなしい

8貧しい人が金持ちにいじめられ、国中で正義が踏みにじられているのを見ても、別に驚くにあたりません。どの役人にも上役がいて、その上にさらに高官がいるからです。それが国の政治の仕組みなのです。 9その全体の上に王が立てられています。その王が国のために献身する王なら、どんなにすばらしいことでしょう。そうした人物だけが国を混乱から救えるのです。

10金銭を愛する者は、決してこれで満足だということがありません。金さえあれば幸せだという考えは、なんと愚かなことでしょう。 11収入が多くなれば、それに応じて支出も多くなります。金銭にどんな利益があるというのでしょう。彼らは金銭が指の間からこぼれ落ちていくのを眺めていることしかできないのです。 12汗水流して働く人は、満腹していようが腹をすかしていようが、ぐっすり眠ることができます。しかし、金満家は不安につきまとわれ、不眠に悩まされます。 13-14私はまた、ここかしこに深刻な問題があるのに気づきました。せっかくの貯金が危険な投資に使われ、子どもに残す財産もなくなってしまうという現実です。 15投機に手を出す者は、すぐさま無一文の振り出しに戻ります。 16これは言ったように、とても深刻な問題です。どんなに働いても、ざるで水をくむようなものであり、風を追うようなものです。せっかく手に入れたものが、全部なくなってしまうのです。 17残る生涯を暗い気持ちで、失意と挫折感、怒りを持ちながら生きることになります。

18でも、良いことが少なくとも一つあります。生きている限りは、おいしい物を食べ、上等のワインを飲み、置かれた立場を受け入れ、与えられた仕事がどのようなものであれ、それを楽しむことです。 19-20主のおかげで財産家になり、健康にも恵まれているとしたら、それこそ申し分のないことです。仕事を楽しみ、与えられた人生に満足することこそ、神からの贈り物です。こういう人は、神から喜びを与えられているのですから、悲しい思いで過去を振り返る必要などありません。