መክብብ 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መክብብ 3:1-22

ለሁሉም ጊዜ አለው

1ለሁሉም ነገር ጊዜ አለው፤

ከሰማይ በታች ለሚከናወነው ለማንኛውም ነገር ወቅት አለው፤

2ለመወለድ ጊዜ አለው፤ ለመሞትም ጊዜ አለው፤

ለመትከል ጊዜ አለው፤ ለመንቀልም ጊዜ አለው፤

3ለመግደል ጊዜ አለው፤ ለማዳንም ጊዜ አለው፤

ለማፍረስ ጊዜ አለው፤ ለመገንባትም ጊዜ አለው፤

4ለማልቀስ ጊዜ አለው፤ ለመሣቅም ጊዜ አለው፤

ለሐዘን ጊዜ አለው፤ ለጭፈራም ጊዜ አለው፤

5ድንጋይ ለመጣል ጊዜ አለው፤ ድንጋይ ለመሰብሰብም ጊዜ አለው፤

ለመተቃቀፍ ጊዜ አለው፤ ለመለያየትም ጊዜ አለው፤

6ለመፈለግ ጊዜ አለው፤ ለመተው ጊዜ አለው፤

ለማስቀመጥ ጊዜ አለው፤ አውጥቶ ለመጣልም ጊዜ አለው፤

7ለመቅደድ ጊዜ አለው፤ ለመስፋትም ጊዜ አለው፤

ለዝምታ ጊዜ አለው፤ ለመናገርም ጊዜ አለው፤

8ለመውደድ ጊዜ አለው፤ ለመጥላትም ጊዜ አለው፤

ለጦርነት ጊዜ አለው፤ ለሰላምም ጊዜ አለው።

9ሠራተኛ ከጥረቱ የሚያገኘው ትርፍ ምንድን ነው? 10ሰዎች ይደክሙበት ዘንድ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ከባድ የሥራ ጫና አየሁ። 11ሁሉንም ነገር በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው፤ በሰዎችም ልብ ዘላለማዊነትን አኖረ፤ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ያደረገውን ማወቅ አይችሉም። 12ለሰዎች፣ በሕይወት እያሉ ደስ ከመሰኘትና መልካምን ነገር ከማድረግ የተሻለ ነገር እንደሌለ ዐወቅሁ። 13ሰው ሁሉ ይበላና ይጠጣ ዘንድ፣ በሚደክምበትም ሁሉ ርካታን ያገኝ ዘንድ ይህ የእግዚአብሔር ችሮታ ነው። 14እግዚአብሔር ያደረገው ሁሉ ለዘላለም እንደሚኖር ዐውቃለሁ፤ በእርሱ ላይ ምንም አይጨመርም፤ ከእርሱም ምንም አይቀነስም፤ ሰዎች ያከብሩት ዘንድ ይህን አደረገ።

15አሁን ያለው ከዚህ በፊት የነበረው ነው፤

ወደ ፊት የሚሆነውም ቀድሞ የነበረ ነው፤

እግዚአብሔርም ያለፈውን መልሶ ይሻዋል3፥15 ወይም እግዚአብሔር ያለፈውን መልሶ ይጠራዋል

16ከፀሓይ በታችም ሌላ ነገር አየሁ፤

በፍርድ ቦታ ዐመፅ ነበር፤

በፍትሕ ቦታ ግፍ ነበር።

17እኔም በልቤ፣

“ለማንኛውም ድርጊት፣

ለማንኛውም ተግባር ጊዜ ስላለው፣

እግዚአብሔር ጻድቁንና ኀጢአተኛውን ወደ ፍርድ ያመጣቸዋል”

ብዬ አሰብሁ።

18እንዲህም ብዬ አሰብሁ፤ “ሰዎች፣ እንደ እንስሳት መሆናቸውን ያዩ ዘንድ እግዚአብሔር ይፈትናቸዋል። 19የሰው ዕድል ፈንታ እንደ እንስሳት ነው፤ ሁለቱም ዕጣ ፈንታቸው አንድ ነው፤ አንዱ እንደሚሞት፣ ሌላውም እንዲሁ ይሞታል። ሁሉ አንድ ዐይነት እስትንፋስ3፥19 ወይም መንፈስ አላቸው፤ ሰውም ከእንስሳ ብልጫ የለውም፤ ሁሉም ከንቱ ነው። 20ሁሉም ወደ አንድ ቦታ ይሄዳሉ፤ ሁሉም ከዐፈር እንደ ሆኑ፣ ተመልሰው ወደ ዐፈር ይሄዳሉ። 21የሰው መንፈስ ወደ ላይ መውጣቱን፣ የእንስሳ እስትንፋስ3፥21 ወይም የሰው መንፈስ ወደ ላይ እንደሚሄድ ወይም የእንስሳት መንፈስ ደግሞ ወደ ታች ወደ ምድር መውረዱን ማን ያውቃል?”

22ስለዚህ ለሰው ዕጣ ፈንታው ስለሆነ፣ በሥራው ከመደሰት የተሻለ ነገር እንደሌለው አየሁ፤ ከእርሱ በኋላ የሚሆነውንስ ተመልሶ እንዲያይ የሚያደርገው ማን ነው?

Thai New Contemporary Bible

ปัญญาจารย์ 3:1-22

มีเวลาสำหรับทุกสิ่ง

1มีเวลาสำหรับทุกสิ่ง

มีกำหนดเวลาสำหรับกิจกรรมทุกอย่าง ภายใต้ฟ้าสวรรค์นี้

2มีเวลาเกิด เวลาตาย

เวลาปลูก เวลาถอน

3เวลาฆ่า เวลาเยียวยารักษา

เวลารื้อถอน เวลาสร้างขึ้นใหม่

4เวลาร้องไห้ เวลาหัวเราะ

เวลาไว้ทุกข์ เวลาเต้นรำ

5เวลาโยนก้อนหิน เวลาเก็บรวบรวมก้อนหิน

เวลาโอบกอด เวลาหันหนี

6เวลาค้นหา เวลาเลิกรา

เวลาทะนุถนอม เวลาเหวี่ยงทิ้งไป

7เวลาฉีกขาด เวลาซ่อมแซม

เวลานิ่งเงียบ เวลาพูดจา

8เวลารัก เวลาเกลียด

เวลาสงคราม เวลาสันติ

9คนเราได้อะไรจากการตรากตรำทำงานหรือ? 10ข้าพเจ้าเห็นภาระซึ่งพระเจ้าทรงวางไว้บนมนุษย์ 11พระองค์ทรงทำให้ทุกสิ่งงดงามตามเวลาของมัน ทั้งทรงตั้งนิรันดร์กาลไว้ในจิตใจของมนุษย์ ถึงอย่างนั้นมนุษย์ก็ไม่สามารถหยั่งรู้ถึงสิ่งที่พระเจ้าทรงทำตั้งแต่ต้นจนจบได้ 12ข้าพเจ้ารู้ว่าสำหรับมนุษย์ไม่มีอะไรดีไปกว่าการทำตัวให้มีความสุข และทำดีขณะยังมีชีวิตอยู่ 13คนเราทุกคนควรกิน ดื่ม และหาความอิ่มใจในการตรากตรำทำงานทั้งสิ้น เพราะนี่คือของขวัญจากพระเจ้า 14ข้าพเจ้ารู้ว่าทุกสิ่งที่พระเจ้าทรงทำจะดำรงอยู่นิรันดร์ ไม่สามารถเพิ่มอะไรเข้าไป หรือตัดทอนอะไรออกได้ พระเจ้าทรงทำไว้เพื่อมนุษย์จะยำเกรงพระองค์

15อะไรก็ตามที่เป็นอยู่ และอะไรที่จะเกิดขึ้น

ก็เป็นอยู่มาก่อนแล้ว

และพระเจ้าจะทรงนำอดีตมาพิพากษาอีก3:15 หรือพระเจ้าจะทรงเรียกอดีตให้หวนกลับมาอีก

16ยิ่งกว่านั้น ภายใต้ดวงอาทิตย์ ข้าพเจ้ายังเห็นอีกว่า

ในที่แห่งการพิพากษาก็มีความชั่วร้ายอยู่ด้วย

ในที่ของความยุติธรรมก็มีความเลวทรามอยู่ด้วย

17ข้าพเจ้ารำพึงว่า

“พระเจ้าจะทรงนำทั้งคนชอบธรรมและคนอธรรมมาพิพากษา

เพราะจะมีเวลาสำหรับทุกเรื่อง

มีเวลาสำหรับการกระทำทุกอย่าง”

18ข้าพเจ้าคิดอีกว่า “สำหรับมนุษย์ พระเจ้าทรงทดสอบพวกเขา ก็เพื่อพวกเขาจะเห็นว่าตนเองก็เหมือนสัตว์ 19ชะตากรรมของมนุษย์ก็เหมือนของสัตว์ ทั้งสองมีอันเป็นไปเหมือนกัน ฝ่ายหนึ่งตาย อีกฝ่ายหนึ่งก็ตาย ต่างก็มีลมปราณ3:19 หรือวิญญาณเช่นกัน มนุษย์ไม่ได้เปรียบมากกว่าสัตว์ ทุกสิ่งล้วนอนิจจัง 20ทั้งสองพวกต่างไปสู่ที่แห่งเดียวกัน ล้วนมาจากธุลีดินและต้องกลับกลายเป็นธุลีดิน 21ใครจะรู้ได้ว่าจิตวิญญาณของมนุษย์ขึ้นไปยังเบื้องบนหรือไม่ และวิญญาณของสัตว์3:21 หรือใครจะรู้จักจิตวิญญาณของมนุษย์ซึ่งขึ้นสู่เบื้องบน หรือวิญญาณของสัตว์ซึ่งลงสู่พิภพโลกหรือไม่?”

22ฉะนั้นข้าพเจ้าเห็นว่าสำหรับมนุษย์แล้ว ไม่มีอะไรดีไปกว่าที่จะสนุกกับงาน เพราะนั่นเป็นส่วนของเขา ใครเล่าจะทำให้เขาเห็นได้ว่าจะมีอะไรเกิดขึ้นหลังจากเขา?