መክብብ 11 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መክብብ 11:1-10

እንጀራ በውሃ ላይ

1እንጀራህን በውሃ ላይ ጣል፤

ከብዙ ቀን በኋላ መልሰህ ታገኘዋለህና።

2ሀብትህን ሰባት ቦታ፣ እንዲያውም ስምንት ቦታ ከፍለህ አስቀምጥ፤

በምድሪቱ ላይ የሚመጣውን ጥፋት አታውቅምና።

3ደመናት ውሃ ካዘሉ፣

በምድር ላይ ዝናብን ያዘንባሉ፤

ዛፍ ወደ ደቡብም ሆነ ወደ ሰሜን ቢወድቅ፣

በወደቀበት ቦታ በዚያ ይጋደማል።

4ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፤

ደመናትንም የሚያይ አያጭድም።

5የነፋስን መንገድ እንደማታውቅ፣

ሕይወት ወይም መንፈስ በእናት ማሕፀን ውስጥ ወደሚገኘው አካል እንዴት እንደሚገባም11፥5 ወይም አካል በእናት ማሕፀን ውስጥ እንዴት እንደሚሠራ እንደማታውቅ ሁሉ እንደማታውቅ ሁሉ፣

ሁሉን ሠሪ የሆነውን፣ የእግዚአብሔርን ሥራ

ማስተዋል አትችልም።

6ጧት ላይ ዘርህን ዝራ፤

ማታም ላይ እጅህ ሥራ አይፍታ፤

ይህ ወይም ያ፣

ወይም ሁለቱ መልካም ይሁኑ፣

የቱ እንደሚያፈራ አታውቅምና።

ወጣት ሳለህ ፈጣሪህን ዐስብ

7ብርሃን መልካም ነው፤

ፀሓይንም ማየት ለዐይን ደስ ያሰኛል።

8ሰው ምንም ያህል ብዙ ዓመት ቢኖር፣

በእነዚህ ሁሉ ይደሰት፤

ነገር ግን ጨለማዎቹንም ቀናት ያስብ፤

እነርሱ ይበዛሉና፤

የሚመጣውም ነገር ሁሉ ከንቱ ነው።

9አንተ ወጣት በወጣትነትህ ጊዜ ደስ ይበልህ፤

በወጣትነትህም ዘመን ልብህ ደስ ያሰኝህ፤

የልብህን መንገድ፣

ዐይንህ የሚያየውንም ሁሉ ተከተል፤

ነገር ግን ስለ እነዚህ ነገሮች ሁሉ፣

እግዚአብሔር ወደ ፍርድ እንደሚያመጣህ ዕወቅ።

10ስለዚህ ጭንቀትን ከልብህ አርቅ፤

ክፉ ነገርንም ከሰውነትህ አስወግድ፤

ወጣትነትና ጕብዝና ከንቱ ናቸውና።

New International Version

Ecclesiastes 11:1-10

Invest in Many Ventures

1Ship your grain across the sea;

after many days you may receive a return.

2Invest in seven ventures, yes, in eight;

you do not know what disaster may come upon the land.

3If clouds are full of water,

they pour rain on the earth.

Whether a tree falls to the south or to the north,

in the place where it falls, there it will lie.

4Whoever watches the wind will not plant;

whoever looks at the clouds will not reap.

5As you do not know the path of the wind,

or how the body is formed11:5 Or know how life (or the spirit) / enters the body being formed in a mother’s womb,

so you cannot understand the work of God,

the Maker of all things.

6Sow your seed in the morning,

and at evening let your hands not be idle,

for you do not know which will succeed,

whether this or that,

or whether both will do equally well.

Remember Your Creator While Young

7Light is sweet,

and it pleases the eyes to see the sun.

8However many years anyone may live,

let them enjoy them all.

But let them remember the days of darkness,

for there will be many.

Everything to come is meaningless.

9You who are young, be happy while you are young,

and let your heart give you joy in the days of your youth.

Follow the ways of your heart

and whatever your eyes see,

but know that for all these things

God will bring you into judgment.

10So then, banish anxiety from your heart

and cast off the troubles of your body,

for youth and vigor are meaningless.