መክብብ 11 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

መክብብ 11:1-10

እንጀራ በውሃ ላይ

1እንጀራህን በውሃ ላይ ጣል፤

ከብዙ ቀን በኋላ መልሰህ ታገኘዋለህና።

2ሀብትህን ሰባት ቦታ፣ እንዲያውም ስምንት ቦታ ከፍለህ አስቀምጥ፤

በምድሪቱ ላይ የሚመጣውን ጥፋት አታውቅምና።

3ደመናት ውሃ ካዘሉ፣

በምድር ላይ ዝናብን ያዘንባሉ፤

ዛፍ ወደ ደቡብም ሆነ ወደ ሰሜን ቢወድቅ፣

በወደቀበት ቦታ በዚያ ይጋደማል።

4ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፤

ደመናትንም የሚያይ አያጭድም።

5የነፋስን መንገድ እንደማታውቅ፣

ሕይወት ወይም መንፈስ በእናት ማሕፀን ውስጥ ወደሚገኘው አካል እንዴት እንደሚገባም11፥5 ወይም አካል በእናት ማሕፀን ውስጥ እንዴት እንደሚሠራ እንደማታውቅ ሁሉ እንደማታውቅ ሁሉ፣

ሁሉን ሠሪ የሆነውን፣ የእግዚአብሔርን ሥራ

ማስተዋል አትችልም።

6ጧት ላይ ዘርህን ዝራ፤

ማታም ላይ እጅህ ሥራ አይፍታ፤

ይህ ወይም ያ፣

ወይም ሁለቱ መልካም ይሁኑ፣

የቱ እንደሚያፈራ አታውቅምና።

ወጣት ሳለህ ፈጣሪህን ዐስብ

7ብርሃን መልካም ነው፤

ፀሓይንም ማየት ለዐይን ደስ ያሰኛል።

8ሰው ምንም ያህል ብዙ ዓመት ቢኖር፣

በእነዚህ ሁሉ ይደሰት፤

ነገር ግን ጨለማዎቹንም ቀናት ያስብ፤

እነርሱ ይበዛሉና፤

የሚመጣውም ነገር ሁሉ ከንቱ ነው።

9አንተ ወጣት በወጣትነትህ ጊዜ ደስ ይበልህ፤

በወጣትነትህም ዘመን ልብህ ደስ ያሰኝህ፤

የልብህን መንገድ፣

ዐይንህ የሚያየውንም ሁሉ ተከተል፤

ነገር ግን ስለ እነዚህ ነገሮች ሁሉ፣

እግዚአብሔር ወደ ፍርድ እንደሚያመጣህ ዕወቅ።

10ስለዚህ ጭንቀትን ከልብህ አርቅ፤

ክፉ ነገርንም ከሰውነትህ አስወግድ፤

ወጣትነትና ጕብዝና ከንቱ ናቸውና።

Het Boek

Prediker 11:1-10

Investeer overvloedig

1Laat uw vermogen over de zeeën varen: na geruime tijd zal het bij u terugkomen. 2Verdeel uw geld over zeven of acht ondernemingen, want u weet niet wat voor onheil er nog komen kan. 3Als de wolken zwaar zijn, komt er regen, een boom blijft liggen waar hij valt. 4Als u steeds blijft wachten op de beste omstandigheden, krijgt u nooit iets gedaan. 5De wegen van God, die alles maakt, zijn net zo ondoorgrondelijk als die van de wind en als de manier waarop het leven groeit in de buik van een vrouw. 6Blijf uw zaad uitzaaien, want u weet nooit welk deel zal gaan groeien, misschien komt alles wel op.

7Het licht is heerlijk, het is een weldaad voor de ogen om de zon te zien schijnen. 8Als iemand een hoge leeftijd bereikt, laat hij dan genieten van elke dag van zijn leven, maar laat hij er ook aan denken dat de eeuwigheid nog veel langer duurt en dat daarbij vergeleken, alles wat hier beneden gebeurt, zeer betrekkelijk is. 9Jongeman, het is heerlijk om jong te zijn! Geniet van elke minuut! Doe alles wat u wilt, pak alles wat u krijgen kunt, maar vergeet niet dat u van alles wat u doet, ook verantwoording moet afleggen tegenover God. 10Ga niet zitten tobben, leef gezond en bedenk dat uw jeugd, net als het morgenrood, snel voorbijgaat.