መሳፍንት 5 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 5:1-31

የዲቦራ መዝሙር

1በዚያን ዕለት ዲቦራና የአቢኒኤም ልጅ ባርቅ ይህን ቅኔ ተቀኙ፤

2“በእስራኤል ያሉ መሳፍንት ሲመሩ፣

ሕዝቡም በፈቃዱ ራሱን ሲያስገዛ፣

እግዚአብሔርን አመስግኑ።

3“እናንት ነገሥታት ይህን ስሙ፤

ገዦችም አድምጡ፤

ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ፤ ደግሜም

ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሴይር በወጣህ ጊዜ፣

ከኤዶም ምድርም በተነሣህ ጊዜ፣

ምድር ተንቀጠቀጠች፤ ሰማያትም ዝናብ አዘነቡ፤

ደመናዎችም ውሃ አፈሰሱ።

5ተራሮች በሲና አምላክ በእግዚአብሔር ፊት፣

በእስራኤልም አምላክ በእግዚአብሔር ፊት ተናወጡ።

6“በዓናት ልጅ በሰሜጋር ዘመን፣

በኢያዔል ጊዜ መንገዶች ባድማ ሆኑ፤

ተጓዦችም በጠመዝማዛ መንገድ ሄዱ።

7ለእስራኤል እናት ሆኜ

እኔ ዲቦራ እስክነሣ ድረስ

በእስራኤል ያለው የከተማ ኑሮ አበቃለት፤

8አዳዲስ አማልክትን በተከተሉ ጊዜ፣

ጦርነት እስከ ከተማው በር መጣ፤

ጋሻም ሆነ ጦር፣

በአርባ ሺሕ እስራኤላውያን መካከል አልተገኘም።

9ልቤ ከእስራኤል መሳፍንት፣

ፈቃደኞችም ከሆኑ ሰዎች ጋር ነው፤

እግዚአብሔር ይመስገን።

10“እናንት በነጫጭ አህዮች የምትጋልቡ፣

በባለ ግላስ ኮርቻ ላይ የምትቀመጡ፣

በመንገድ ላይ የምትጓዙ፣

በውሃ ምንጮች ዙሪያ ያለውን፣

11የዝማሬ ድምፅ5፥11 ወይም ቀስተኞች ተብሎ ሊተረጐም ይችላል። ስሙ።

ይህም የእግዚአብሔር የጽድቅ ሥራ፣

ጦረኞቹም በእስራኤል ያደረጉትን ያስታውሳል።

“ከዚያም የእግዚአብሔር ሕዝቦች፣

ወደ ከተማዪቱ5፥11 ወይም ወደ መንደሮቹ ተብሎ መተርጐም ይቻላል። በሮች ወረዱ።

12‘ዲቦራ ሆይ፤ ንቂ፤ ንቂ፤

ንቂ፤ ንቂ፤ ቅኔም ተቀኚ፤

የአቢኒኤል ልጅ ባራቅ ሆይ፤ ተነሣ፤

ምርኮኞችህንም ማርከህ ውሰድ’ አሉ።

13“የቀሩትም ሰዎች፣

ወደ መኳንንቱ ወረዱ፤ የእግዚአብሔር ሕዝብ፣ እንደ ኀያል ጦረኛ ወደ እኔ መጣ።

14መሠረታቸው ከአማሌቅ የሆነ አንዳንዶች

ከኤፍሬም መጡ፤ ብንያም አንተን ከተከተሉ ሰዎች ጋር ነበር፤

የጦር አዛዦች ከማኪር፣

የሥልጣን በትር የያዙም ከዛብሎን ወረዱ።

15የይሳኮር መሳፍንት ከዲቦራ ጋር ነበሩ፤

ይሳኮርም ራሱ ወደ ሸለቆው ከኋላው

በመከተል፣ ከባርቅ ጋር ነበረ።

በሮቤል አውራጃዎች፣ ብዙ የልብ

ምርምር ነበር።

16በበጎች ጕረኖ5፥16 ወይም በኮርቻ ላይ ተብሎ መተርጐም ይቻላል። መካከል ለምን ተቀመጥህ?

መንጎችን የሚጠራውን ፉጨት ለመስማት ነውን?

በሮቤል አውራጃዎች፣ ብዙ የልብ

ምርምር ነበር።

17ገለዓድ ከዮርዳኖስ ማዶ ተቀመጠ፤

ዳን ለምን በመርከብ ውስጥ ዘገየ?

አሴር በጠረፍ ቀረ፤

በባሕሩ ዳርቻም ተቀመጠ።

18የዛብሎን ሰዎች ሕይወታቸውን አሳልፈው ሰጡ፤

የንፍታሌም ሰዎች እንደዚሁ በምድሪቱ ኰረብታዎች አደረጉ።

19“ነገሥታት መጡ፤ ተዋጉም፤

የከነዓን ነገሥታት፣ በመጊዶ ውሆች

አጠገብ በታዕናክ ተዋጉ፤

ብርም ሆነ ሌላ ምርኮ ተሸክመው አልሄዱም።

20ከሰማያት ከዋክብት ተዋጉ፤

በአካሄዳቸውም ሲሣራን ገጠሙት።

21ጥንታዊው ወንዝ፣ የቂሶን ወንዝ፣

የቂሶን ወንዝ ጠርጎ ወሰዳቸው፤

ነፍሴ ሆይ፤ በኀይል ገሥግሺ

22የፈረሶች ኰቴ ድምፅ በኀይል ተሰማ፤

ጋለቡ፤ በኀይልም ፈጥነው ጋለቡ።

23የእግዚአብሔር መልአክ፣ ‘ሜሮዝን ርገሙ፤’

‘ሕዝቧንም አብራችሁ ርገሙ፤

ከኀያላን ሰልፍ እግዚአብሔርን ለመርዳት፣

በእግዚአብሔርም ጐን ለመቆም አልመጡምና’ አለ።

24“የቄናዊው የሔቤር ሚስት ኢያዔል፣

ከሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን፤

በድንኳን ከሚኖሩ ሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን።

25ውሃ ለመነ፤ ወተት ሰጠችው፤

ለመኳንንት በሚገባ ዕቃ፣ እርጎ አቀረበችለት።

26እጇ ካስማ ያዘ፤

ቀኝ እጇም የሠራተኛ መዶሻ ጨበጠ፤

ሲሣራን መታችው፤ ራሱንም ተረከከችው፤

ክፉኛ ወጋችው፤ ጆሮ ግንዱን በሳችው።

27በእግሯ ሥር ተደፋ፤ ወደቀ፤

በዚያም ተዘረረ፤ በእግሯ ሥር ተደፋ፤

ወደቀ፤ በተደፋበት በዚያ ወደቀ፤

ሞተም።

28“የሲሣራ እናት በመስኮት ተመለከተች፤

በዐይነ ርግቡ ቀዳዳም ጮኻ ተጣራች፤

‘ለምን ሠረገላው ሳይመጣ ዘገየ?

የሠረገሎቹስ ድምፅ ለምን ጠፋ?’ አለች።

29ብልኅተኞች ወይዛዝርቷም መለሱላት፤

እርሷ ግን ለራሷ እንዲህ አለች፤

30‘ምርኮ አግኝተው እየተከፋፈሉ፣

እያንዳንዱም ሰው አንዲት ወይም ሁለት ልጃገረዶች እየወሰደ አይደለምን?

ይህ ሁሉ ምርኮ፣ በቀለም ያጌጡ ልብሶች

ለሲሣራ ደርሰውት፣

በጌጣጌጥ የተጠለፉ ልብሶች ለዐንገቴ

ይዞልኝ እየመጣ አይደለምን?’

31“እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶችህ ሁሉ ይጥፉ፤

አንተን የሚወድዱህ ግን፣ የንጋት ፀሓይ

በኀይል እንደሚወጣ እንዲያ ይሁኑ።”

ከዚያም በኋላ ምድሪቱ ለአርባ ዓመት ሰላም አገኘች።

New International Version

Judges 5:1-31

The Song of Deborah

1On that day Deborah and Barak son of Abinoam sang this song:

2“When the princes in Israel take the lead,

when the people willingly offer themselves—

praise the Lord!

3“Hear this, you kings! Listen, you rulers!

I, even I, will sing to5:3 Or of the Lord;

I will praise the Lord, the God of Israel, in song.

4“When you, Lord, went out from Seir,

when you marched from the land of Edom,

the earth shook, the heavens poured,

the clouds poured down water.

5The mountains quaked before the Lord, the One of Sinai,

before the Lord, the God of Israel.

6“In the days of Shamgar son of Anath,

in the days of Jael, the highways were abandoned;

travelers took to winding paths.

7Villagers in Israel would not fight;

they held back until I, Deborah, arose,

until I arose, a mother in Israel.

8God chose new leaders

when war came to the city gates,

but not a shield or spear was seen

among forty thousand in Israel.

9My heart is with Israel’s princes,

with the willing volunteers among the people.

Praise the Lord!

10“You who ride on white donkeys,

sitting on your saddle blankets,

and you who walk along the road,

consider 11the voice of the singers5:11 The meaning of the Hebrew for this word is uncertain. at the watering places.

They recite the victories of the Lord,

the victories of his villagers in Israel.

“Then the people of the Lord

went down to the city gates.

12‘Wake up, wake up, Deborah!

Wake up, wake up, break out in song!

Arise, Barak!

Take captive your captives, son of Abinoam.’

13“The remnant of the nobles came down;

the people of the Lord came down to me against the mighty.

14Some came from Ephraim, whose roots were in Amalek;

Benjamin was with the people who followed you.

From Makir captains came down,

from Zebulun those who bear a commander’s5:14 The meaning of the Hebrew for this word is uncertain. staff.

15The princes of Issachar were with Deborah;

yes, Issachar was with Barak,

sent under his command into the valley.

In the districts of Reuben

there was much searching of heart.

16Why did you stay among the sheep pens5:16 Or the campfires; or the saddlebags

to hear the whistling for the flocks?

In the districts of Reuben

there was much searching of heart.

17Gilead stayed beyond the Jordan.

And Dan, why did he linger by the ships?

Asher remained on the coast

and stayed in his coves.

18The people of Zebulun risked their very lives;

so did Naphtali on the terraced fields.

19“Kings came, they fought,

the kings of Canaan fought.

At Taanach, by the waters of Megiddo,

they took no plunder of silver.

20From the heavens the stars fought,

from their courses they fought against Sisera.

21The river Kishon swept them away,

the age-old river, the river Kishon.

March on, my soul; be strong!

22Then thundered the horses’ hooves—

galloping, galloping go his mighty steeds.

23‘Curse Meroz,’ said the angel of the Lord.

‘Curse its people bitterly,

because they did not come to help the Lord,

to help the Lord against the mighty.’

24“Most blessed of women be Jael,

the wife of Heber the Kenite,

most blessed of tent-dwelling women.

25He asked for water, and she gave him milk;

in a bowl fit for nobles she brought him curdled milk.

26Her hand reached for the tent peg,

her right hand for the workman’s hammer.

She struck Sisera, she crushed his head,

she shattered and pierced his temple.

27At her feet he sank,

he fell; there he lay.

At her feet he sank, he fell;

where he sank, there he fell—dead.

28“Through the window peered Sisera’s mother;

behind the lattice she cried out,

‘Why is his chariot so long in coming?

Why is the clatter of his chariots delayed?’

29The wisest of her ladies answer her;

indeed, she keeps saying to herself,

30‘Are they not finding and dividing the spoils:

a woman or two for each man,

colorful garments as plunder for Sisera,

colorful garments embroidered,

highly embroidered garments for my neck—

all this as plunder?’

31“So may all your enemies perish, Lord!

But may all who love you be like the sun

when it rises in its strength.”

Then the land had peace forty years.