የእግዚአብሔር መልአክ በቦኪም
1የእግዚአብሔር መልአክ ከጌልገላ ወደ ቦኪም ወጥቶ እንዲህ አለ፤ “ከግብፅ ምድር አወጣኋችሁ፤ ለቀደሙትም አባቶቻችሁ ልሰጣቸው ወደ ማልሁላቸው ምድር አመጣኋችሁ፤ እንዲህም አልሁ፤ ከእናንተ ጋር የገባሁትን ቃል ኪዳኔን አላፈርስም፤ 2እናንተም ከዚህች ምድር ነዋሪዎች ጋር ቃል ኪዳን አታድርጉ፤ መሠዊያቸውንም አፍርሱ፤ እናንተ ግን አልታዘዛችሁኝም፤ ይህን ያደረጋችሁት ለምንድን ነው? 3ስለዚህ አሁንም ከፊታችሁ አሳድጄ እንደማላስወጣቸው እነግራችኋለሁ፤ ነገር ግን እነርሱ የጐን ውጋት፣ አማልክታቸውም ወጥመድ ይሆኑባችኋል።”
4የእግዚአብሔርም መልአክ ይህን ቃል ለእስራኤላውያን ሁሉ በተናገረ ጊዜ፣ ሕዝቡ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው አለቀሱ፤ 5ያንን ስፍራ ቦኪም2፥5 ቦኪም ማለት አልቃሽ ማለት ነው። ብለው ጠሩት፤ በዚያም ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አቀረቡ።
ያለ መታዘዝ ውጤት
6ኢያሱ ሕዝቡን ካሰናበተ በኋላ እያንዳንዱ የእስራኤል ነገድ ምድሪቱን ለመውረስ ወደየርስቱ ሄደ። 7ኢያሱ በሕይወት በነበረበት ዘመን ሁሉ እንዲሁም ከእርሱ በኋላ እግዚአብሔር ለእስራኤል ያደረገውን ታላላቅ ነገሮች ሁሉ ያዩ አለቆች በነበሩበት ዘመን ሁሉ ሕዝቡ እግዚአብሔርን አመለከ።
8የእግዚአብሔር አገልጋይ የነዌ ልጅ ኢያሱ በመቶ ዐሥር ዓመቱ ሞተ። 9እነርሱም በኰረብታማው በኤፍሬም አገር በምትገኘው ከገዓስ ተራራ በስተ ሰሜን ባለችው በራሱ ርስት ላይ በተምናሔሬስ ቀበሩት።
10ያ ሁሉ ትውልድ ወደ አባቶቹ ከተከማቸ በኋላ እግዚአብሔርንም ሆነ እርሱ ለእስራኤል ሕዝብ ያደረገውን ነገር የማያውቅ ሌላ ትውልድ ተነሣ። 11ከዚያም እስራኤላውያን በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ነገር አደረጉ፤ የበኣል አማልክትንም አመለኩ። 12ከግብፅ ምድር ያወጣቸውን የአባቶቻቸውን አምላክ እግዚአብሔርን ተዉ፤ በዙሪያቸው ያሉት ሕዝቦች የሚያመልኳቸውን አማልክት ተከተሉ፤ ሰገዱላቸውም። እግዚአብሔርንም አስቈጡት፤ 13እርሱን ትተው በኣልንና አስታሮትን አምልከዋልና 14እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ በመቈጣቱ ለሚዘርፏቸው አሳልፎ ሰጣቸው፤ በዙሪያቸው ላሉ ጠላቶቻቸው ሸጣቸው። 15እስራኤላውያን ለውጊያ በሚወጡበት ጊዜ ሁሉ እግዚአብሔር አስቀድሞ በእነርሱ ላይ እንደ ተናገረውና እንደ ማለው ይሸነፉ ዘንድ የእግዚአብሔር እጅ ትከፋባቸው ነበር፤ ከዚህም የተነሣ እጅግ ተጨነቁ።
16እግዚአብሔርም ከእነዚህ ወራሪዎች የሚያድኗቸውን መሳፍንት2፥16 በዚህም ከ17-19 ባለው ክፍል መሪ ተብሎ ሊተረጐም ይችላል። አስነሣ፤ 17እስራኤላውያን ግን ሌሎችን አማልክት ተከትለው አመነዘሩ፤ ሰገዱላቸውም እንጂ መሳፍንታቸውን አልሰሙም። አባቶቻቸው እግዚአብሔርን በመታዘዝ በሄዱበት መንገድ ሳይሆን፣ አባቶቻቸው የእግዚአብሔርን ሕግ በመከተል ከሄዱበት መንገድ ፈጥነው ፈቀቅ አሉ። 18እግዚአብሔር መሳፍንትን ባሰነሣላቸው ቍጥር ከመስፍኑ ጋር ስለሚሆን፣ እርሱ በሕይወት እስካለ ድረስ እግዚአብሔር ከጠላቶቻቸው ያድናቸው ነበር፤ ከጠላቶቻቸው ሥቃይና መከራ ሲደርስባቸው በሚጮኹበት ጊዜ እግዚአብሔር ይራራላቸው ነበር። 19መስፍኑ ከሞተ በኋላ ግን ሕዝቡ ሌሎችን አማልክት በመከተል፣ እነርሱን በማገልገልና በማምለክ ከአባቶቻቸው ይልቅ ወደ ክፉ መንገድ ተመለሱ፤ ክፉ ሥራቸውንና የእልኸኝነት መንገዳቸውንም አይተውም ነበር።
20ስለዚህ እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ እጅግ ተቈጣ፤ እንዲህም አለ፤ “ይህ ሕዝብ ለቀደሙ አባቶቹ የሰጠሁትን ቃል ኪዳን ስለ ተላለፈ፣ እኔንም ስላልሰማ፣ 21ኢያሱ በሞተ ጊዜ ከተዋቸው በምድሪቱ ከነበሩት ሕዝቦች አንዳቸውንም እንኳ በፊታቸው አሳድጄ አላስወጣም። 22ይህን የማደርገውም አባቶቻቸው እንዳደረጉት ሁሉ፣ እስራኤላውያን የእግዚአብሔርን መንገድ የሚጠብቁ መሆን አለመሆናቸውን ለማወቅ እፈትናቸው ዘንድ እነርሱን መሣሪያ ለማድረግ ነው።” 23ስለዚህ እግዚአብሔር እነዚያን ሕዝቦች በዚያው እንዲኖሩ አደረገ፤ በኢያሱ እጅ አሳልፎ በመስጠት ወዲያውኑ አሳድዶ አላስወጣቸውም።
فرشتهٔ خداوند در بوكيم
1-2روزی فرشتهٔ خداوند از جلجال به بوكيم آمده، به قوم اسرائيل گفت: «من شما را از مصر به سرزمينی كه وعدهٔ آن را به اجدادتان دادم آوردم و گفتم كه هرگز عهدی را كه با شما بستهام نخواهم شكست، به شرطی كه شما نيز با اقوامی كه در سرزمين موعود هستند هم پيمان نشويد و قربانگاههای آنها را خراب كنيد؛ ولی شما اطاعت نكرديد. 3پس من نيز اين قومها را از اين سرزمين بيرون نمیكنم و آنها چون خار به پهلوی شما فرو خواهند رفت و خدايان ايشان چون تله شما را گرفتار خواهند كرد.»
4وقتی فرشته سخنان خود را به پايان رسانيد، قوم اسرائيل با صدای بلند گريستند. 5آنها آن مكان را بوكيم (يعنی «آنانی كه میگريند») ناميده، در آنجا برای خداوند قربانی كردند.
مرگ يوشع
6يوشع قوم اسرائيل را پس از ختم سخنرانی خود مرخص كرد و آنها رفتند تا زمينهايی را كه به ايشان تعلق میگرفت، به تصرف خود درآورند. 7-9يوشع خدمتگزار خداوند، در سن صد و ده سالگی درگذشت و او را در ملكش در تمنه حارس واقع در كوهستان افرايم به طرف شمال كوه جاعش به خاک سپردند. قوم اسرائيل در طول زندگانی يوشع و نيز ريشسفيدان قوم كه پس از او زنده مانده بودند و شخصاً اعمال شگفتانگيز خداوند را در حق اسرائيل ديده بودند، نسبت به خداوند وفادار ماندند.
بنیاسرائيل از خداوند روگردان میشوند
10ولی بالاخره تمام مردم آن نسل مردند و نسل بعدی خداوند را فراموش كردند و هر آنچه كه او برای قوم اسرائيل انجام داده بود، به ياد نياوردند. 11ايشان نسبت به خداوند گناه ورزيدند و به پرستش بتها روی آوردند. 12-14آنها خداوند، خدای پدران خود را كه ايشان را از مصر بيرون آورده بود، ترک نموده، بتهای طايفههای همسايهٔ خود را عبادت و سجده میكردند. بنابراين خشم خداوند بر تمام اسرائيل افروخته شده و ايشان را به دست دشمنانشان سپرد تا غارت شوند، زيرا او را ترک نموده، بتهای بعل و عشتاروت را عبادت میكردند.
15هرگاه قوم اسرائيل با دشمنان میجنگيدند، خداوند بر ضد اسرائيل عمل میكرد، همانطور كه قبلاً در اين مورد هشدار داده و قسم خورده بود. اما وقتی كه قوم به اين وضع فلاكتبار دچار گرديدند 16خداوند رهبرانی فرستاد تا ايشان را از دست دشمنانشان برهانند. 17ولی از رهبران نيز اطاعت ننمودند و با پرستش خدايان ديگر، نسبت به خداوند خيانت ورزيدند. آنها برخلاف اجدادشان عمل كردند و خيلی زود از پيروی خداوند سر باز زده، او را اطاعت ننمودند. 18هر يک از رهبران در طول عمر خود، به كمک خداوند قوم اسرائيل را از دست دشمنانشان میرهانيد، زيرا خداوند به سبب نالهٔ قوم خود و ظلم و ستمی كه بر آنها میشد، دلش بر آنها میسوخت و تا زمانی كه آن رهبر زنده بود به آنها كمک میكرد. 19اما وقتی كه آن رهبر میمرد، قوم به كارهای زشت خود برمیگشتند و حتی بدتر از نسل قبل رفتار میكردند. آنها باز به سوی خدايان بتپرستان روی آورده، جلو آنها زانو میزدند و آنها را عبادت مینمودند و با سرسختی به پيروی از رسوم زشت بتپرستان ادامه میدادند.
20پس خشم خداوند بر بنیاسرائيل افروخته شد و فرمود: «چون اين قوم پيمانی را كه با پدران ايشان بستم شكستهاند و از من اطاعت نكردهاند، 21من نيز قبايلی را كه هنگام فوت يوشع هنوز مغلوب نشده بودند، بيرون نخواهم كرد. 22بلكه آنها را برای آزمودن قوم خود میگذارم تا ببينم آيا آنها چون پدران خود، مرا اطاعت خواهند كرد يا نه.»
23پس خداوند آن قبايل را در سرزمين كنعان واگذاشت. او ايشان را توسط يوشع به کلی شكست نداده بود و بعد از مرگ يوشع نيز فوری آنها را بيرون نكرد.