መሳፍንት 18 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 18:1-31

ዳናውያን ሰዎች በላይሽ ሰፈሩ

1በዚያን ዘመን በእስራኤል ንጉሥ አልነበረም፤ የዳን ነገድም በእስራኤል ነገዶች መካከል ርስተ ድርሻውን ገና ስላልወሰደ፣ የሚሰፍርበትን የራሱን ርስት ይፈልግ ነበር። 2ስለዚህ ዳናውያን ምድሪቱን እንዲሰልሉና እንዲመረምሩ አምስት ኀያላን ሰዎች ከጾርዓና ከኤሽታኦል ከተሞች ወደዚያ ላኩ፤ እነዚህም ነገዶቻቸውን ሁሉ የሚወክሉ ነበሩ። የላኳቸውም ሰዎች፣ “ሂዱ፤ ምድሪቱን ሰልሉ” አሏቸው።

መልእክተኞቹም ወደ ኰረብታማው የኤፍሬም አገር ገቡ፤ ወደሚያድሩበትም ወደ ሚካ ቤት መጡ። 3በሚካ ቤት አጠገብ እንደ ደረሱም የወጣቱን ሌዋዊ ድምፅ ዐወቁ፤ ስለዚህ ወደዚያ ጐራ ብለው፣ “ወደዚህ ያመጣህ ማን ነው? እዚህ ምን ትሠራለህ? የመጣኸውስ ለምንድን ነው?” ሲሉ ጠየቁት።

4እርሱም፣ “ሚካ ይህን አደረገልኝ፤ ቀጠረኝ፤ ካህኑም ሆንሁ” አላቸው።

5እነርሱም፣ “መንገዳችን መቃናት አለመቃናቱን እንድናውቅ እባክህ እግዚአብሔርን ጠይቅልን” አሉት።

6ካህኑም፣ “በሰላም ሂዱ፤ መንገዳችሁን እግዚአብሔር አቃንቶላችኋል” ብሎ መለሰላቸው።

7ስለዚህ አምስቱ ሰዎች ከዚያ ተነሥተው ወደ ላይሽ መጡ፤ ሲዶናውያን ያለ ሥጋት በጸጥታ18፥7 በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጉም በትክክል አይታወቅም። እንደሚኖሩ ሁሉ፣ በዚያም የሚኖረው ሕዝብ በሰላም እንደሚኖር አዩ። ምድሪቱ አንዳች የሚጐድላት ነገር ባለመኖሩ ሕዝቡ ባለጠጋ ነበር። እንዲሁም ከሲዶናውያን ርቆ የሚኖር ሲሆን፣ ከማንኛውም ሕዝብ ጋር18፥7 በዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ሲስማማ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን ከአራም ስዎች ጋር ይላል። ግንኙነት አልነበረውም።

8ወደ ጾርዓና ወደ ኤሽታኦል እንደ ተመለሱ ወገኖቻቸው፣ “የሄዳችሁበት ጕዳይ እንዴት ሆነ?” በማለት ጠየቋቸው።

9መልእክተኞቹም እንዲህ አሏቸው፤ “ምድሪቱ እጅግ መልካም መሆኗን አይተናል፤ እንግዲህ ተነሡ! ሄደን እንዋጋቸው፤ ተነሡ እንጂ ዝም ትላላችሁን? ወደዚያው ሄዳችሁ ምድሪቱን ለመያዝ አታመንቱ፤ 10እዚያ ስትደርሱም ያለ ሥጋት የሚኖር ሕዝብ፣ እግዚአብሔር በእጃችሁ የሚሰጣችሁን አንዳች ነገር ያልጐደላትን ሰፊ ምድር ታገኛላችሁ።”

11ከዚያ በኋላም ከዳን ወገን ለጦርነት ዝግጁ የሆኑ ስድስት መቶ ሰዎች ከጾርዓና ከኤሽታኦል ተነሡ። 12ወጥተውም በይሁዳ ምድር ባለችው በቂርያትይዓሪም ሰፈሩ፤ እንግዲህ ከቂርያትይዓሪም በስተ ምዕራብ ያለው ስፍራ እስከ ዛሬ ድረስ የዳን ሰፈር መባሉ ከዚሁ የተነሣ ነው። 13ከዚያም ተጕዘው ወደ ኰረብታማው የኤፍሬም አገር በመሄድ ወደ ሚካ ቤት መጡ።

14የላይሽን ምድር ሰልለው የነበሩት አምስቱ ሰዎች ለወንድሞቻቸው፣ “ከእነዚሁ ቤቶች በአንዱ ኤፉድ፣ ተራፊም፣ የተቀረጸ ምስልና ቀልጦ የተሠራ ጣዖት እንዳለ ታውቃላችሁን? እንግዲህ ምን ማድረግ እንዳለባችሁ ዕወቁበት” አሏቸው። 15ስለዚህ ወጣቱ ሌዋዊ ወደሚኖርበት ወደ ሚካ ቤት ጐራ ብለው ሰላምታ አቀረቡለት። 16ለጦርነት ተዘጋጅተው የመጡት ስድስት መቶ የዳን ሰዎች በቅጥሩ በር መግቢያ ላይ ቆመው ነበር። 17ካህኑ ለጦርነት ከተዘጋጁት ስድስት መቶ ሰዎች ጋር በቅጥሩ በር ላይ ቆሞ ሳለ፣ ምድሪቱን ለመሰለል መጥተው የነበሩትን አምስት ሰዎች ወደ ቤቱ ውስጥ በመግባት የተቀረጸውን ምስልና ኤፉዱን፣ ተራፊሙንና ቀልጦ የተሠራውን ምስል ወሰዱ።

18እነዚህ ሰዎች ወደ ሚካ ቤት ገብተው የተቀረጸውን ምስልና ኤፉዱን፣ ተራፊሙንና ቀልጦ የተሠራውን ምስል በሚወስዱበት ጊዜ ካህኑ፣ “ምን ማድረጋችሁ ነው?” አላቸው።

19እነርሱም፣ “ዝም በል! አንዲት ቃል እንዳትተነፍስ፤ ከእኛ ጋር ሁን፤ አባትም ካህንም ሁነን፤ ለአንተስ የአንድ ቤተ ሰብ ካህን ከመሆን ይልቅ በእስራኤል የአንዱ ነገድና ጐሣ ካህን ሆነህ ማገልገሉ አይሻልህምን?” አሉት። 20ይህም ካህኑን ደስ አሰኘው፤ እርሱም ኤፉዱን፣ ተራፊሙንና የተቀረጸውን ምስል ይዞ ከሕዝቡ ጋር ሄደ። 21እነርሱም ሕፃናታቸውን፣ የከብቶቻቸውን መንጋና ሀብታቸውን ሁሉ ወደ ፊት በማስቀደም ተመልሰው ሄዱ።

22ከሚካ ቤት ጥቂት ራቅ እንዳሉም፣ የሚካ ጎረቤቶች ለርዳታ ተጠርተው ተሰበሰቡ፤ የዳን ሰዎችንም ተከታትለው ደረሱባቸው። 23ከበሰተ ኋላቸው ሆነው ሲጮኹባቸውም፣ የዳን ሰዎች ወደ ኋላቸው ዞረው ሚካን፣ “ሰዎችህን ለውጊያ አሰባስበህ መምጣትህ ምን ሆንህና ነው?” አሉት።

24እርሱም፣ “እንዴት፣ ‘ምን ሆንህ’ ብላችሁ ትጠይቁኛላችሁ? የሠራኋቸውን አማልክቴንና ካህኔን ወስዳችሁ ሄዳችኋል፤ ምን የቀረኝ ነገር አለ?” አላቸው።

25የዳን ሰዎች፣ “አትሟገተን፤ ያለዚያ የተቈጡ ሰዎች ጕዳት ላይ ይጥሉሃል፤ አንተም ቤተ ሰብህም ሕይወታችሁን ታጣላችሁ” አሉት። 26የዳን ሰዎች ይህን ብለው መንገዳቸውን ቀጠሉ፤ ሚካም የማይችላቸው መሆኑን በማየት ተመልሶ ወደ ቤቱ ሄደ።

27ከዚያም ሚካ የሠራውን ጣዖትና ካህኑን ወስደው ወደ ላይሽ በመሄድ፣ በሰላምና ያለ ሥጋት ይኖር የነበረውን ሕዝብ በሰይፍ መቱት፤ ከተማዪቱንም በእሳት አቃጠሏት። 28የሚኖሩት ከሲዶና በጣም ርቀው ስለ ነበርና ከማንም ጋር ግንኙነት ስላልነበራቸው የሚታደጋቸው አንድም አልነበረም፤ ከተማዪቱም የምትገኘው በቤትሮዓብ አጠገብ ነበረ።

የዳንም ሰዎች ከተማዪቱን እንደ ገና ሠርተው መኖሪያቸው አደረጓት። 29ከተማዪቱንም ከእስራኤል በተወለደው በአባታቸው በዳን ስም ዳን ብለው ጠሯት፤ ቀድሞ ግን ስሟ ላይሽ ይባል ነበር። 30እዚያም የዳን ሰዎች ለራሳቸው ጣዖታት አቆሙ፤ የሙሴ ልጅ፣18፥30 ጥንታዊው የዕብራውያን ጸሐፍት ትውፊት፣ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም እንዲሁም የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን ምናሴ ይላል። የጌርሳም ልጅ ዮናታንና የእርሱም ልጆች ምድሪቱ እስከ ተማረከችበት ጊዜ ድረስ ለዳን ነገድ ካህናት ሆኗቸው፤ 31ስለዚህም ሚካ የሠራቸውን ጣዖታት፣ የእግዚአብሔር ቤት በሴሎ በነበረበት ጊዜ ሁሉ ባለማቋረጥ አመለኳቸው።

Bibelen på hverdagsdansk

Dommerbogen 18:1-31

Dans stamme stjæler Mikas afgudsbilleder

1På den tid var der som sagt ingen konge i Israel. Dans stamme søgte efter et sted, hvor de kunne slå sig ned, eftersom det endnu ikke var lykkedes dem at indtage det område, de havde fået tildelt. 2De udvalgte fem tapre krigere som repræsentanter for deres forskellige klaner fra byerne Zora og Eshtaol. De blev sendt af sted for at udspionere hele landet. I Efraims højland overnattede de i Mikas hus. 3Da de hørte den unge levits dialekt, gik de hen til ham og spurgte: „Hvordan er du kommet herhen? Hvad laver du her?” 4Så fortalte han dem, hvordan Mika havde taget imod ham og ansat ham som sin personlige præst.

5„Bed så Gud om at vise os, om vores ærinde vil lykkes!” sagde de. 6Præsten svarede: „Vær ved godt mod! Herren vil være med jer på rejsen!”

7Derefter fortsatte de fem mænd til byen Lajish. De så, at byens folk levede ubekymret i fred og sikkerhed ligesom sidonierne, at de var velstående og ikke manglede noget, og at de boede langt fra Sidon og ingen kontakt havde med de omkringboende aramæere.

8Da spionerne kom tilbage til Zora og Eshtaol, spurgte deres stammefæller dem: „Hvordan gik det? Hvad fandt I ud af?” 9-10Mændene svarede: „Lad os tage af sted og erobre Lajish! Vi har set, at landet er virkelig godt. Der er ikke noget at betænke sig på. Folket dér lever fredeligt og bekymrer sig ikke om noget, for de mangler intet. Gud har givet os et frugtbart og rummeligt land.”

11Så rykkede danitterne op fra Zora og Eshtaol med en hær på 600 bevæbnede krigere, 12og de slog lejr ved det sted vest for Kirjat-Jearim i Juda, som den dag i dag kaldes Dans Lejr. 13Derfra gik de ind i Efraims højland.

Da de kom til Mikas hus, 14sagde spionerne til krigerne: „I gudehuset derhenne er der en efod, nogle husguder, et gudebillede og en støbt gudestatuette. Mon ikke vi er enige om, hvad vi skal gøre?”

15-16Så gik de fem mænd hen til gudehuset, mens de 600 krigere blev stående uden for porten. Da den unge præst kom ud til porten, hilste mændene hjerteligt på ham. 17Mens præsten stod udenfor sammen med krigerne, kom de fem mænd ud fra Mikas gudehus med gudebilledet, efoden, husguderne og den støbte gudestatuette. 18„Hvad er det, I gør?” udbrød præsten forbavset. 19„Ti stille og følg med!” svarede de. „Fra nu af skal du være vejleder og præst for os! Er det ikke bedre at være præst for en hel stamme end bare for en enkelt mand?” 20Det forslag syntes præsten godt om, og uden yderligere indvendinger tog han efoden, husguderne og gudebilledet og fulgte med dem.

21Hele gruppen fortsatte nu rejsen mod Lajish med deres børn, kvæg og ejendele forrest. 22Da de var kommet lidt på afstand, tilkaldte Mika sine naboer og satte efter dem, der havde stjålet hans guder. Da de havde indhentet dem, 23råbte de til dem, at de skulle standse.

„Hvad er der i vejen?” spurgte danitterne. „Hvorfor kommer du med alle de folk?” 24„Hvad tror I?” råbte Mika tilbage. „I har stjålet mine guder og min præst, så nu har jeg ingenting tilbage. Og så spørger I, hvad der er i vejen!” 25„Du gør bedst i at passe dig selv!” svarede danitterne. „Ellers kunne det være, at nogle af os blev sure og huggede jer alle sammen ned!”

26Da Mika blev klar over, at der ikke var noget at stille op, vendte han om og gik hjem, og danitterne fortsatte deres rejse 27-28med hans afgudsbilleder og hans præst.

Da de nåede frem til Lajish, der lå fredeligt og trygt i dalen ved Bet-Rehob, huggede de indbyggerne ned og brændte byen af. Der var ingen, der kom til undsætning, afstanden til Sidon var for stor, og de havde ingen kontakt med de omkringboende aramæere. Efter sejren genopbyggede danitterne byen og blev boende der. 29De gav byen et nyt navn og opkaldte den efter deres forfar Dan, en af Jakobs sønner.

30Derefter opstillede de afgudsbillederne i byen og udnævnte Jonatan fra Gershoms slægt18,30 Teksten siger: „Gershom, søn af Moses”, men nogle håndskrifter siger „Manasse” i stedet for Moses. Jonatan er sikkert den føromtalte levit. til præst. Jonatans efterkommere vedblev at være præster for danitterne, indtil byens befolkning blev ført bort som fanger til et fjendtligt land. 31Danitterne brugte Mikas afgudsbilleder, imens Herrens helligdom var i Shilo.