መሳፍንት 17 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 17:1-13

ሚካ ያሠራቸው ጣዖታት

1ሚካ የተባለ በኰረብታማው በኤፍሬም አገር የሚኖር ሰው ነበር። 2እናቱን፣ “አንድ ሺሕ አንድ መቶ ሰቅል17፥2 13 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብር ተሰርቆብሽ፣ የሰረቀውን ሰው ስትራገሚ ሰምቼሽ ነበር፤ ብሩ ከእኔ ዘንድ ይገኛል፤ የወሰድሁት እኔ ነኝ” አላት።

ከዚያም እናቱ፣ “ልጄ፤ እግዚአብሔር ይባርክህ” አለችው።

3አንድ ሺሕ አንድ መቶውን ሰቅል ብር በመለሰላት ጊዜ እናቱ፣ “ብሬን የተቀረጸ ምስልና ቀልጦ የተሠራ ጣዖት ለማበጀት ስለ ልጄ ለእግዚአብሔር እቀድሰዋለሁ፤ አሁንም ለአንተው መልሼ እሰጥሃለሁ” አለችው።

4ስለዚህ ብሩን ለእናቱ መለሰላት፤ እናቱም ከላዩ ሁለት መቶ ጥሬ17፥4 17፥4 2.3 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብር ወስዳ ለብር አንጥረኛ ሰጠች፤ አንጥረኛውም የተቀረጸ ምስልና ቀልጦ የተሠራ ጣዖት አደረገው፤ ምስሎቹም በሚካ ቤት ተቀመጡ።

5ሚካ የተባለው ይህ ሰው የአምልኮ ስፍራ ነበረው፤ አንድ ኤፉድና ተራፊም ሠርቶ ከልጆቹ አንዱን ካህን ሆኖ እንዲያገለግለው አደረገ። 6በዚያን ዘመን በእስራኤል ንጉሥ አልነበረም፤ እያንዳንዱ ሰው ለራሱ መልካም መስሎ የታየውን ያደርግ ነበር። 7በይሁዳ ምድር፣ በይሁዳ ነገድ መካከል በቤተ ልሔም የሚኖር አንድ ሌዋዊ ወጣት ነበር። 8ይህም ሰው ሌላ መኖሪያ ስፍራ ለመፈለግ ከተማዪቱን ለቆ ሄደ። በሚጓዝበትም17፥8 ወይም የዕለት ምግባሩን እያከናወነ ሳለ ጊዜ በኰረብታማው በኤፍሬም አገር ወዳለው ወደ ሚካ ቤት መጣ።

9ሚካም፣ “የየት አገር ሰው ነህ?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፣ “እኔ በይሁዳ ምድር ከምትገኝ ከቤተ ልሔም የመጣሁ ሌዋዊ ነኝ፤ መኖሪያ ስፍራ እፈልጋለሁ” አለው።

10ሚካም፣ “እንግዲያውስ አብረኸኝ ተቀመጥ፤ አባትም ካህንም ሁነኝ፤ እኔም በዓመት ዐሥር ሰቅል17፥10 110 ግራም ያህል ነው። ብር እንዲሁም ልብስና ምግብ እሰጥሃለሁ” አለው። 11ስለዚህ ሌዋዊው አብሮት ለመኖር ተስማማ፤ ወጣቱም ለሚካ ከልጆቹ እንደ አንዱ ሆነለት። 12ሚካም ሌዋዊውን ካህን አድርጎ አስቀመጠው፤ ወጣቱም ካህኑ ሆነ፤ በቤቱም ኖረ። 13ሚካም፤ “ይህ ሌዋዊ ካህን ለሆነልኝ፣ እግዚአብሔር በጎ ነገር እንደሚያደርግልኝ አሁን ተረዳሁ” አለ።

Thai New Contemporary Bible

ผู้วินิจฉัย 17:1-13

เทวรูปของมีคาห์

1ในแดนเทือกเขาแห่งเอฟราอิม มีชายคนหนึ่งชื่อมีคาห์ 2เขากล่าวกับมารดาว่า “เงินหนัก 1,100 เชเขล17:2 1 เชเขล คือเงินหนักประมาณ 11.5 กรัม มีค่าเท่ากับค่าแรงสองเดือน เช่นเดียวกับข้อ 3,4 และ 10ที่แม่คิดว่าถูกขโมยไปและข้าพเจ้าได้ยินแม่สาปแช่งขโมยอยู่ ที่แท้ข้าพเจ้าเอาไปเอง”

มารดาก็ตอบว่า “ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอวยพรลูกเถิด!”

3เมื่อเขาคืนเงินหนัก 1,100 เชเขลแก่มารดาของเขา นางกล่าวว่า “แม่จะเอาเงินนี้ไปถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าสำหรับลูก แม่จะทำรูปสลักและหล่อรูปเคารพให้ลูก”

4ดังนั้นเขาจึงคืนเงินให้แก่มารดาและนางนำเงินหนัก 200 เชเขล ไปให้ช่างเงินทำรูปเคารพขึ้นมาตั้งไว้ที่บ้านของมีคาห์

5มีคาห์คนนี้มีหิ้งบูชา เขาทำเอโฟดและรูปเคารพต่างๆ และตั้งบุตรชายคนหนึ่งของตนให้เป็นปุโรหิต 6ในสมัยนั้นอิสราเอลไม่มีกษัตริย์ปกครองทุกคนต่างทำตามที่ตนเองเห็นดีเห็นชอบ

7มีหนุ่มเลวีคนหนึ่งซึ่งอาศัยอยู่ในเขตของตระกูลยูดาห์ มาจากเบธเลเฮมในยูดาห์ 8เขาจากที่นั่นมาเพื่อหาที่พักอาศัยแห่งใหม่ ระหว่างทาง17:8 หรือเพื่อมาประกอบอาชีพของเขาต่อไปเขามาถึงบ้านของมีคาห์ในแดนเทือกเขาแห่งเอฟราอิม

9มีคาห์ถามเขาว่า “ท่านมาจากไหน?”

เขาตอบว่า “ข้าพเจ้าเป็นคนเลวีมาจากเบธเลเฮมในแผ่นดินยูดาห์ กำลังหาที่พักอาศัย”

10มีคาห์จึงกล่าวว่า “มาอยู่กับข้าพเจ้าเถิด มาเป็นบิดาและเป็นปุโรหิตของข้าพเจ้า ข้าพเจ้าจะให้เงินท่านปีละ 10 เชเขลพร้อมทั้งเสื้อผ้าและอาหาร” 11ดังนั้นหนุ่มเลวีจึงตกลงอยู่กับเขา เขาเป็นเหมือนบุตรชายคนหนึ่งของมีคาห์ 12จากนั้นมีคาห์แต่งตั้งชายหนุ่มเลวีผู้นั้นให้เป็นปุโรหิตอาศัยอยู่ในบ้านของเขา 13และมีคาห์กล่าวว่า “บัดนี้ข้าพเจ้ารู้แล้วว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงดีต่อข้าพเจ้า เพราะว่าชาวเลวีคนนี้มาเป็นปุโรหิตของข้าพเจ้า”