መሳፍንት 14 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 14:1-20

የሳምሶን ጋብቻ

1ሳምሶን ወደ ተምና ወረደ፤ እዚያም አንዲት ወጣት ፍልስጥኤማዊት አየ። 2እንደ ተመለሰም አባቱንና እናቱን፣ “በተምና አንዲት ወጣት ፍልስጥኤማዊት አይቻለሁና አሁኑኑ አጋቡኝ” አላቸው።

3አባቱና እናቱም፣ “ከዘመዶችህ ወይም ከሕዝባችን ሁሉ መካከል ለአንተ የምትሆን ሴት መች ታጣችና ነው ወዳልተገረዙት ፍልስጥኤማውያን ሚስት ፍለጋ የሄድኸው?” አሉት።

ሳምሶንም አባቱን፣ “ልቤን የማረከችው እርሷ ናትና እርሷን አጋባኝ” አለው። 4በዚያን ጊዜ በእስራኤል ላይ ገዦቹ ፍልስጥኤማውያን ስለ ነበሩ፣ ከፍልስጥኤማውያን ጋር ጠብ እንዲፈጠር እግዚአብሔር ሆን ብሎ ያደረገው ነገር መሆኑን አባቱና እናቱ አላወቁም ነበር። 5ከዚያም ሳምሶን ከአባቱና ከእናቱ ጋር ወደ ተምና ወረደ፤ በዚያም ከአንድ የወይን አትክልት ቦታ እንደ ደረሱ፣ ድንገት አንድ የአንበሳ ደቦል እያገሣ መጣበት። 6በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር መንፈስ በኀይል ወረደበት፤ ስለዚህ የፍየል ጠቦት እንደሚገነጣጠል አንበሳውን ያለ ምንም መሣሪያ በባዶ እጁ ገነጣጠለው፤ ያደረገውን ግን ለአባቱም ሆነ ለእናቱ አልነገራቸውም ነበር። 7ወደ ሴቲቱም ወረደ፤ ከእርሷም ጋር ተነጋገረ፤ እጅግም ወደዳት።

8ከጥቂት ቀን በኋላም ሊያገባት ተመለሰ። የአንበሳውንም በድን ለማየት ከመንገድ ዘወር አለ፤ በበድኑም ውስጥ የንብ መንጋ ሰፍሮ ተመለከተ፤ ማርም ነበረበት፤ 9በእጁ ወስዶም መንገድ ለመንገድ እየበላ ሄደ፤ ከወላጆቹም ጋር እንደ ተገናኘም ከማሩ ሰጣቸው፤ እነርሱም በሉ። ነገር ግን ማሩን የወሰደው ከአንበሳ በድን መሆኑን አልነገራቸውም ነበር።

10የሳምሶን አባት ልጂቱን ሊያይ ወረደ፤ ሳምሶንም በነበረው የሙሽራ ወግ መሠረት በዚያ ግብዣ አደረገ። 11እርሱም ለፍልስጥኤማውያን በታየ ጊዜ፣ ሠላሳ አጃቢዎች ሰጡት።

12ሳምሶን እንዲህ አላቸው፤ “አንድ ዕንቈቅልሽ እነግራችኋለሁ፤ ታዲያ ፍቺውን በሰርጉ በዓል ሰባት ቀኖች ውስጥ ከሰጣችሁኝ፣ ሠላሳ የቀጭን ፈትል በፍታ ቀሚስና ሠላሳ የክት ልብስ እሰጣችኋለሁ። 13ዕንቈቅልሹን ካልፈታችሁልኝ ግን ሠላሳ የቀጭን ፈትል በፍታ ቀሚስና ሠላሳውን የክት ልብስ እናንተ ትሰጡኛላችሁ።”

እነርሱም፣ “በል ዕንቈቅልሽህን ንገረንና እንስማው” አሉት።

14ሳምሶንም፣

“ከበላተኛው መብል፣

ከብርቱም ጣፋጭ ነገር ወጣ” አላቸው።

እነርሱም እስከ ሦስት ቀን ድረስ እንቈቅልሹን መፍታት አልቻሉም ነበር።

15በአራተኛው14፥15 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና የሱርስቱ ትርጕም ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን ሰባተኛ ይላል። ቀን የሳምሶንን ሚስት፣ “የዕንቈቅልሹን ፍች እንዲነግረን ባልሽን እስቲ አግባቢልን፤ ያለዚያ አንቺንም የአባትሽንም ቤተ ሰብ በእሳት እናቃጥላችኋለን፤ ጠርታችሁ የጋበዛችሁን ልትዘርፉን ነው?” አሏት።

16ከዚያ የሳምሶን ሚስት ተንሰቅስቃ እያለቀሰች ከፊቱ በመቅረብ፣ “ለካስ ትጠላኛለህ! በርግጥ አትወደኝም” አለችው።

እርሱም፣ “ይህን ለአባቴም ሆነ ለእናቴ አልነገርኋቸውም፤ ታዲያ ለአንቺ ለምን እነግርሻለሁ?” አላት። 17ሚስቱም በሰርጉ በዓል ሰባት ቀን ሙሉ እያለቀሰች ጨቀጨቀችው፤ አጥብቃ ስለ ነዘነዘችውም በመጨረሻ በሰባተኛው ቀን ነገራት፤ እርሷም በበኩሏ የዕንቈቅልሹን ፍች ለሕዝቧ ነገረች።

18በሰባተኛው ቀን ፀሓይ ከመጥለቋ በፊት የከተማው ሰዎች፣

“ከማር የጣፈጠ ምን ተገኝቶ?

ከአንበሳስ ወዲያ ብርቱ ከየት መጥቶ!” አሉት።

ሳምሶንም መልሶ፣

“በጊደሬ ባላረሳችሁ፣

እንቈቅልሼንም ባልፈታችሁ” አላቸው።

19ከዚያም የእግዚአብሔር መንፈስ በሳምሶን ላይ በኀይል ወረደበት፤ ወደ አስቀሎናም ወርዶ ከሰዎቻቸው መካከል ሠላሳውን ገደለ፤ ያላቸውንም ከገፈፈ በኋላ ልብሶቻቸውን አምጥቶ እንቈቅልሹን ለፈቱት ሰዎች ሰጣቸው። በቍጣ እንደ ነደደም ተነሥቶ ወደ አባቱ ቤት ወጣ። 20የሳምሶንም ሚስት ለሚዜው ተዳረች።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

士師記 14:1-20

參孫娶非利士女子為妻

1參孫下到亭拿,在那裡看中了一個非利士女子。 2他回到家裡便對父母說:「我在亭拿看中一個非利士女子,把她給我娶來做妻子吧!」 3他父母說:「難道我們的親族和同胞中,沒有一個令你滿意的女子嗎?你為什麼要娶未受割禮的非利士人的女子呢?」參孫卻說:「我很喜歡她,請給我把她娶過來吧!」

4他的父母不知道這事是出於耶和華的旨意,祂要找機會對付非利士人。那時,非利士人統治著以色列

5參孫跟父母一起去亭拿,走到亭拿的葡萄園時,有一頭壯獅吼叫著撲向他。 6耶和華的靈降在參孫身上,他雖然手無寸鐵,竟撕裂了那頭獅子,就像撕裂一隻山羊羔一樣。他沒有把這事告訴父母。 7到了亭拿參孫跟那女子交談,很喜歡她。 8過了些日子,參孫下去迎娶她,途中他順便去看那隻死獅子,見死獅子體內有一群蜜蜂和一些蜂蜜, 9就用手取了一些蜜,邊走邊吃。到了父母那裡,他給了他們一些,他們也吃了。但他沒有告訴父母蜂蜜是從死獅子體內取的。

10參孫的父親去那女子家,參孫按習俗擺設宴席。 11眾人看見參孫,就安排了三十個人陪他。 12參孫對他們說:「我出一個謎語,如果你們可以在這七天的婚宴期間猜出來,我就送你們三十件細麻衣和三十件外袍。 13如果猜不中,你們就要給我三十件細麻衣和三十件外袍。」他們說:「請你出謎語吧!」 14參孫說:

「食物出自食者,

甜物出自強者。」

三天過後,他們仍然猜不出來。

15到了第四天,他們對參孫的妻子說:「你要哄你的丈夫把謎底說出來,不然我們就把你和你父親一家全燒死。你們邀請我們來,難道是要叫我們傾家蕩產嗎?」 16於是,參孫的妻子向他哭訴說:「你是恨我,不是愛我。你給我的族人出了謎語,卻沒有告訴我謎底。」參孫回答說:「我連父母都沒有告訴,又怎能告訴你呢?」 17在七天的婚宴期間,她一直在丈夫跟前哭哭啼啼。到了第七天,參孫經不住妻子的催逼就把謎底告訴了她。她把謎底告訴了她的族人。 18在第七天日落之前,城裡的人對參孫說:

「有什麼比蜂蜜更甜?

有什麼比獅子更強?」

參孫說:

「你們若不是利用我的小母牛耕田,

肯定猜不出來。」

19耶和華的靈降在參孫身上,他便去亞實基倫殺了三十個人,擄走他們的衣服,交給猜中謎語的那些人,然後怒氣沖沖地回父親家去了。 20參孫的妻子後來歸了他的伴郎。