ሕዝቅኤል 7 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 7:1-27

ፍጻሜው ደረሰ

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“አንተ የሰው ልጅ ሆይ፤ ጌታ እግዚአብሔር ለእስራኤል ምድር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ፍጻሜ! በአራቱም የምድሪቱ ማእዘን

ፍጻሜ መጥቷል!

3አሁንም መጨረሻሽ ደርሷል፤

ቍጣዬን በአንቺ ላይ አፈስሳለሁ፤

እንደ አካሄድሽ እፈርድብሻለሁ፤

ስለ ጸያፍ ተግባርሽ ሁሉ፣

ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ።

4በርኅራኄ ዐይን አልመለከትሽም፤

ምሕረትም አላደርግልሽም፤

ስለ አካሄድሽና በመካከልሽ ስላለው ጸያፍ ተግባር፣

ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ፤

በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።’

5“ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘መዓት! ተሰምቶ የማይታወቅ መዓት7፥5 አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች እንዲሁ ናቸው፤ አንዳንድ የዕብራይስጥና የሱርስት የጥንት ቅጆች ግን በጥፋት ላይ ጥፋት ይላሉ ይመጣል።

6ፍጻሜ መጥቷል!

ፍጻሜ መጥቷል!

በአንቺ ላይ ተነሣሥቷል፤

እነሆ፤ ደርሷል!

7እናንት በምድሪቱ የምትኖሩ ሆይ፤

የጥፋት ፍርድ መጥቶባችኋል፤

ጊዜው ደርሷል፤

በተራሮች ላይ እልልታ ሳይሆን ሽብር የሚሰማበት ቀን ቀርቧል።

8እነሆ፤ መዓቴን በቅርብ ቀን አፈስስብሻለሁ፤

በአንቺ ላይ ቍጣዬን እፈጽምብሻለሁ፤

እንደ አካሄድሽ እፈርድብሻለሁ፤

ስለ ጸያፍ ተግባርሽም ሁሉ ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ።

9በርኅራኄ ዐይን አልመለከትሽም፤

ምሕረት አላደርግልሽም፤

ስለ አካሄድሽና በመካከልሽ ስላለው ጸያፍ ተግባር፣

ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ፤

በዚያ ጊዜ፣ የምቀሥፍ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን ታውቃላችሁ።

10“ ‘እነሆ ቀኑ ይኸው ደረሰ!

የጥፋት ፍርድ ተገልጧል፤

በትሩ አቈጥቍጧል፤

ትዕቢት አብቧል።

11ዐመፅ ዐድጋ7፥11 ወይም ዐመፀኛው የክፋት በትር

የክፋት በትር ሆነች፤

ከሕዝቡ አንድም አይተርፍም፤

ከሰዎቹ፣

ከሀብታቸውና እርባና ካለው ነገር

አንዳች አይቀርም።

12ጊዜው ደርሷል፤

ቀኑም ይኸው!

መዓት በሕዝቡ ሁሉ ላይ ስለ መጣ፣

የሚገዛ አይደሰት፤

የሚሸጥም አይዘን።

13ሁለቱ በሕይወት እስካሉ ድረስ

ሻጩ የሸጠውን መሬት አያስመልስም፤

ስለ መላው ሕዝብ የተነገረው ራእይ አይለወጥምና።

ከኀጢአታቸው የተነሣ ሕይወቱን ማትረፍ የሚችል አንድም አይገኝም።

14“ ‘መለከት ቢነፉም፣

ሁሉንም ነገር ቢያዘጋጁም፣

ወደ ጦርነት የሚሄድ አንድ እንኳ አይኖርም፤

መዓቴ በሕዝብ ሁሉ ላይ መጥቷልና።

15በውጭ ሰይፍ፣

በውስጥ ደግሞ ቸነፈርና ራብ አለ፤

በገጠር ያሉት

በሰይፍ ይወድቃሉ፤

በከተማ ያሉትም

በራብና በቸነፈር ያልቃሉ።

16ተርፈው ያመለጡት ሁሉ

በሸለቆ እንደሚኖሩ ርግቦች

ስለ ኀጢአታቸው እያለቀሱ

በተራራ ላይ ይሆናሉ።

17እጅ ሁሉ ይዝላል፤

ጕልበት ሁሉ ውሃ ይሆናል።

18ማቅ ይለብሳሉ፤

ሽብርም ይውጣቸዋል።

ፊታቸው ኀፍረት ይለብሳል፤

ራሳቸውም ይላጫል።

19“ ‘ብራቸውን በየጐዳናው ይጥላሉ፤

ወርቃቸውም እንደ ርኩስ ነገር ይቈጠራል።

በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን

ብራቸውና ወርቃቸው

ሊያድናቸው አይችልም፤

በኀጢአት እንዲወድቁ ዕንቅፋት ሆኖባቸዋልና

በልተው አይጠግቡበትም፤ ሆዳቸውንም አይሞሉበትም።

20በውብ ዕንቋቸው ታብየዋል፤

ይህንም አስጸያፊ የጣዖት ምስሎቻቸውንና

ርኩስ ቅርጻ ቅርጾችን ለመሥራት ተጠቅመውበታል።

ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ወደ ርኩሰት እለውጥባቸዋለሁ።

21ለባዕዳን ዝርፊያ፣ ለምድር ክፉዎችም ብዝበዛ አድርጌ አሳልፌ እሰጣለሁ፤

እነርሱም ያረክሱታል።

22ፊቴን ከእነርሱ እመልሳለሁ፤

እነርሱም የከበረውን ቦታዬን ያረክሳሉ፤

ወንበዴዎች ይገቡበታል፤

ያረክሱታልም።

23“ ‘ምድር በደም መፋሰስ፣

ከተማዪቱም በዐመፅ ተሞልታለችና

ሰንሰለት አዘጋጅ።

24እጅግ የከፉትን ከአሕዛብ አምጥቼ

ቤቶቻቸውን እንዲነጥቁ አደርጋለሁ፣

የኀያላኑንም ትዕቢት አጠፋለሁ፤

መቅደሳቸውም ይረክሳል።

25ሽብር በመጣ ጊዜ ሰላምን ይሻሉ፤

ነገር ግን አያገኟትም።

26ጥፋት በጥፋት ላይ፣

ወሬም በወሬ ላይ ይመጣል።

ራእይን ከነቢይ ለማግኘት ይጥራሉ፤

የሕግ ትምህርት ከካህኑ፣

ምክርም ከሽማግሌው ዘንድ ይጠፋል።

27ንጉሡ ያለቅሳል፤

መስፍኑ ተስፋ መቍረጥን ይከናነባል፤

የምድሪቱም ሕዝብ እጅ ትንቀጠቀጣለች።

የእጃቸውን እከፍላቸዋለሁ፤

ራሳቸው ባወጡት መስፈርት መሠረት

እፈርድባቸዋለሁ።

በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以西结书 7:1-27

以色列的结局近了

1耶和华对我说: 2“人子啊,主耶和华对以色列这样说,‘结局到了,以色列全境的结局到了! 3以色列,你的结局到了,我的怒气必倾倒在你身上,我必按你的行为审判你,照你的一切恶行报应你。 4我必不顾惜你,也不怜悯你,我必按你的恶行报应你。这样,你必知道我是耶和华。’”

5主耶和华说:“看啊,灾祸来了,一场空前的灾祸来了! 6结局到了,结局到了,你的结局到了! 7以色列境内的居民啊,恶运降临了!时候已到,日子已近,山上一片恐慌,欢乐荡然无存。 8我快要向你倾倒我的烈怒,发出我的怒气。我必按你的行为审判你,照你一切的恶行报应你。 9我必不顾惜你,也不怜悯你,我必按你的恶行报应你。这样,你就知道惩罚你的是我耶和华。

10“看啊,看啊,日子到了,大祸临头了!杖已经发芽,傲慢已经开花。 11暴行成了惩罚邪恶的杖,以色列人必没有一个能够存留,他们的财富和尊荣必不复存在。 12时候到了,日子近了,买主不要欢乐,卖主也不要忧愁,因为烈怒临到了所有的人。 13即使卖主活着,也无法赎回他所卖的,因为关乎每一个人的异象必然应验,他们因为犯罪一个也不能保存性命。

14“他们吹响了号角,做好了一切准备,却无人出战,因为我的烈怒临到了所有的人。 15城外有战祸,城内有饥荒瘟疫;城外的必丧身刀下,城内的必死于饥荒瘟疫。 16侥幸逃到山上的,都必像谷中哀鸣的鸽子,为自己的罪恶哭泣。 17他们必吓得两手发软,双腿战抖。 18他们必身披麻衣,战栗发抖。他们必剃光头发,满面羞愧。 19他们必把银子抛在街上,视金子为污秽之物。在耶和华发烈怒的日子,金银不能拯救他们,也不能填饱他们的肚腹,满足他们的心,因为金银使他们跌入罪恶中。 20他们以华美的饰物为骄傲,并用它制造丑恶可憎的神像,因此,我必使这一切变成他们眼中的污秽之物。 21我必使这一切成为外族人手中的猎物,恶人手中的战利品,被任意糟蹋。 22我必转脸不看他们,任由外族人亵渎我的殿,强盗必进入殿里大肆亵渎。

23“你要预备锁链,因为这地方充满了血腥的罪恶,城里充斥着暴行。 24我必让最凶恶的外族人侵占他们的房屋。我必挫掉强悍之人的傲气,使他们的圣所遭受亵渎。 25恐怖的日子来临了,他们想寻求平安,却得不到平安。 26灾祸接踵而至,噩耗不断传来。那时,他们必求问先知,但祭司的教导必消逝,长老们必无计可施。 27君王必悲哀,首领必惊恐,百姓的手都必颤抖。我必按他们的恶行对付他们,使他们受到应得的审判。这样,他们就知道我是耶和华。”