ሕዝቅኤል 5 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 5:1-17

1“አንተም፤ የሰው ልጅ ሆይ፤ የተሳለ ሰይፍ ወስደህ እንደ ጢም መላጫ ጠጕርህንና ጢምህን ተላጭበት፤ ጠጕሩንም በሚዛን ከፋፍል። 2የከበባው ጊዜ ሲፈጸም የጠጕሩን ሢሶ በከተማው ውስጥ አቃጥለው፤ ሌላውን ሢሶ ጠጕር በከተማዪቱ ዙሪያ ሁሉ በሰይፍ ቈራርጠው፤ የቀረውንም ሢሶ ደግሞ ለነፋስ በትነው፤ እኔም በተመዘዘ ሰይፍ አሳድዳቸዋለሁና። 3ደግሞም ከጠጕሮቹ ጥቂት ወስደህ በመጐናጸፊያህ ጫፍ ቋጥር፤ 4እንደገናም ከእነዚህ ጥቂት ወስደህ እሳት ውስጥ ጨምራቸው፤ አቃጥላቸውም። እሳትም ከዚያ ወጥቶ ወደ እስራኤል ቤት ሁሉ ይሠራጫል።

5“ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘አገሮችን በዙሪያዋ ሁሉ አድርጌ፣ በአሕዛብም መካከል ያስቀመጥኋት ኢየሩሳሌም ይህች ናት። 6እርሷም በዙሪያዋ ካሉት አገሮችና አሕዛብ ይልቅ በሕጌና በሥርዐቴ ላይ በክፋቷ ዐመፀች፤ ሕጌን ጥላለች፤ ሥርዐቴንም አልተከተለችም።’

7“ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በዙሪያችሁ ካሉት አሕዛብ ይልቅ ሞገደኞች ሆናችኋል፤ ሥርዐቴን አልተከተላችሁም፤ ለሕጌም አልታዘዛችሁም። በዙሪያችሁ የሚገኙ አሕዛብ የሚጠብቁትን ሕግ እንኳ አልጠበቃችሁም።’5፥7 አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆችና አንዳንድ የዕብራይስጥና የሱርስት የጥንት ቅጆች የሚጠብቁትን ሕግ ጠብቃችኋል ይላሉ።

8“ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እነሆ፤ እኔ ራሴ በአንቺ ላይ ተነሥቻለሁ፤ በአሕዛብም ፊት ፍርድ አመጣብሻለሁ። 9በጸያፍ ተግባርሽ ሁሉ ምክንያት ካሁን ቀደም ያላደረግሁትን፣ ወደ ፊትም የማላደርገውን በአንቺ ላይ አደርጋለሁ። 10ስለዚህ በመካከልሽ አባቶች ልጆቻቸውን፣ ልጆችም አባቶቻቸውን ይበላሉ፤ ፍርድንም አመጣብሻለሁ፤ ከአንቺ የተረፉትንም ለነፋስ እበትናለሁ።’ 11ስለዚህ በሕያውነቴ እምላለሁ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ መቅደሴን በረከሱ ምስሎችሽና በጸያፍ ተግባርሽ ሁሉ ስላጐደፍሽ፣ ፊቴን ከአንቺ እመልሳለሁ፤ በርኅራኄ አልመለከትሽም፤ አልምርሽም። 12ከሕዝብሽ ሢሶው በቸነፈር ይሞታል፤ በመካከልሽም በራብ ያልቃል፤ ሌላው ሢሶ ከቅጥርሽ ውጪ በሰይፍ ይወድቃል፤ የቀረውን ሢሶ ደግሞ ለነፋስ እበትናለሁ፤ በተመዘዘም ሰይፍ አሳድደዋለሁ።

13“ከዚያም ቍጣዬ ይበርዳል፤ በእነርሱ ላይ የመጣው መቅሠፍቴ ይመለሳል፤ ስበቀላቸው እረካለሁ፤ በእነርሱም ላይ መዓቴን ካወረድሁ በኋላ፣ እኔ እግዚአብሔር በቅናት እንደ ተናገርሁ ያውቃሉ።

14“በዙሪያሽ ባሉ አሕዛብ መካከል፤ በአጠገብሽም በሚያልፉ ሁሉ ፊት ባድማና መሳለቂያ አደርግሻለሁ። 15በቍጣና በመዓት፣ እንዲሁም በጭካኔ ፍርድ በማመጣብሽ ጊዜ፣ በዙሪያሽ ባሉ አሕዛብ ዘንድ የመሣቂያና የመሣለቂያ፣ የተግሣጽና የማስደንገጫ ምልክት ትሆኛለሽ። እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ። 16የሚገድለውንና አጥፊ የሆነውን የራብ ፍላጻ በእናንተ ላይ በምወረውርበት ጊዜ በርግጥ ላጠፋችሁ እሰድዳለሁ። በራብ ላይ ራብ አመጣባችኋለሁ፤ የምግብ ምንጫችሁንም አደርቃለሁ። 17ራብንና የዱር አራዊትን እሰድድባችኋለሁ፤ እነርሱም ልጅ አልባ ያደርጓችኋል። ቸነፈርና ደም መፋሰስ ያጥለቀልቃችኋል፤ ሰይፍንም አመጣባችኋለሁ፤ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以西结书 5:1-17

1“人子啊,去拿一把快刀当作剃头刀,剃掉你的头发和胡须,然后用天平把须发平均分成三份。 2围城期满后,你要把三分之一的须发焚烧在城中,三分之一在城的四周用刀砍断,三分之一要扬在风中吹散,因为我要拔刀追杀他们。 3你要从须发中取出几缕用衣服包上, 4再从中取出几根丢在火里焚烧,必有火从这里燃起,蔓延到整个以色列。”

5主耶和华说:“这就是耶路撒冷!我把她安置在万邦的中央,使列国环绕着她。 6但她违背我的典章,作恶甚于列邦,触犯我的律例甚于她周围的列国。他们拒绝我的典章,不遵守我的律例。” 7所以主耶和华说:“你们比周围的国家更混乱不堪,你们没有遵行我的律例,不谨守我的典章,连周围的国家都不如。” 8因此主耶和华这样说:“看啊,我要对付你们,我必在列国面前审判你们。 9因为你们一切的恶行,我必向你们施行空前绝后的惩罚。 10在你们中间,父亲要吃自己的儿子,儿子要吃自己的父亲。我必惩罚你们,把你们余下的人分散到各地各方。” 11主耶和华说:“因为你们用一切可憎的偶像和恶行玷污我的圣所,我凭我的永恒起誓,我必毫不留情地铲除你们。 12你们三分之一的人要死于饥荒瘟疫,三分之一的人要死于刀下,我必把其余的三分之一分散到各地各方,并拔刀追杀他们。 13这样,我对你们的怒气才会发完,我才会息怒。我把烈怒倾倒在你们身上的时候,你们就会知道我耶和华的话是出于痛恨不贞。 14我必使你们的家园在周围的列国中,在路人眼前成为荒凉之地,使你们饱受羞辱。 15当我在气愤和烈怒中严厉地审判你们时,你们在各国必受羞辱和嘲讽,成为警戒,下场可怕。这是我耶和华说的。 16我要向你们射出饥荒的毒箭,破坏和毁灭你们,并且使饥荒越来越严重,断绝你们的粮源。 17我必让饥荒和猛兽来侵害你们,夺走你们的儿女,使你们饱受瘟疫、暴行和刀剑之灾,这是我耶和华说的。”