ሕዝቅኤል 42 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 42:1-20

ለካህናት የተመደቡ ክፍሎች

1ከዚያም ያ ሰው በሰሜን በኩል ወዳለው ወደ ውጩ አደባባይ በማምጣት፣ በቤተ መቅደሱ አደባባይ ትይዩና በሰሜን በኩል ባለው ግንብ ትይዩ ወደ አሉት ክፍሎች አመጣኝ። 2በሩ በሰሜን ትይዩ የሆነው ሕንጻ ርዝመቱ አንድ መቶ ክንድ ወርዱም አምሳ ክንድ ነበር። 3ከውስጠኛው አደባባይ ሃያ ክንድ ርቀት ላይና በአንጻሩም ከውጩ አደባባይ የንጣፍ ድንጋይ ፊት ለፊት ርቀት ላይ በሦስት ደርቦች ትይዩ የሆኑ ሰገነቶች ነበሩ። 4ከክፍሎቹ ፊት ለፊት ወርዱ ዐሥር ክንድ፣ ርዝመቱ አንድ መቶ ክንድ42፥4 ሰብዐ ሊቃናቱና ሱርስቱ እንዲሁ ሲሆኑ ዕብራይስጡ ግን …አንድ ክንድ ይላል የሆነ መተላለፊያ በውስጥ በኩል ነበር። የክፍሎቹም በሮች በሰሜን በኩል ነበሩ። 5የላይኞቹ ክፍሎች ጠበብ ያሉ ናቸው፤ ምክንያቱም ሰገነቶቹ ታችና መካከል ላይ ካሉት ከሕንጻው ክፍሎች ይልቅ ሰፋ ያሉ ቦታዎች ይዘውባቸዋልና። 6አደባባዮቹ ዐምዶች ሲኖሯቸው፣ በሦስተኛው ደርብ ላይ ያሉት ክፍሎች ግን ዐምድ የላቸውም። ስለዚህ የወለላቸው ስፋት በታችኛውና በመካከለኛው ደርብ ካሉት ክፍሎች ይልቅ ጠበብ ያለ ነው። 7ከክፍሎቹና፣ ከውጩ አደባባይ ትይዩ የሆነ የውጪ ግንብ አለ፤ ይህም በክፍሎቹ ፊት ለፊት ሆኖ አምሳ ክንድ ይረዝማል። 8ከውጩ አደባባይ ቀጥሎ ያሉት መደዳ ክፍሎች ርዝመት አምሳ ክንድ ሲሆን፣ ከቤተ መቅደሱ አጠገብ ያሉት መደዳ ክፍሎች ርዝመት ደግሞ አንድ መቶ ክንድ ነበር። 9ከውጩ አደባባይ ወደ ውስጥ ሲገባ፣ በስተ ምሥራቅ የታችኞቹ ክፍሎች መግቢያ ይገኛል።

10በደቡብ በኩል42፥10 ሰብዐ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን በስተ ምሥራቅ ይላል የውጩን አደባባይ ግንብ ተከትሎ፣ ከቤተ መቅደሱ አደባባይ ጋር የተያያዙና ከውጩ ግንብ ጋር ትይዩ የሆኑ ክፍሎች አሉ፤ 11ከፊት ለፊታቸውም መተላለፊያ መንገድ አለ። እነዚህ በሰሜን በኩል ካሉት ክፍሎች ጋር ተመሳሳይ ሲሆኑ፣ ርዝመትና ወርዳቸው፣ መውጫና መጠናቸው አንድ ዐይነት ነበር፤ በሰሜን በኩል እንዳሉት በሮች፣ 12በደቡብ በኩል ያሉት ክፍሎች በሮች መጠናቸው ተመሳሳይ ነበር። ከመመላለሻው መነሻ ላይ መግቢያ በር አለ፤ መመለሻውም ፊት ለፊት ካለው ወደ ምሥራቅ ከሚያመራው ግንብ ጋር ተጓዳኝ ነው።

13ከዚያም እንዲህ አለኝ፤ “ከቤተ መቅደሱ አደባባይ ፊት ለፊት ያሉት የሰሜኑና የደቡቡ ክፍሎች የካህናቱ ሲሆኑ፣ እነዚህም በእግዚአብሔር ፊት የሚቀርቡት ካህናት እጅግ የተቀደሱትን ቍርባኖች የሚበሉባቸው ናቸው። በዚያም እጅግ የተቀደሱትን ቍርባኖች ማለት የእህሉን ቍርባን፣ የኀጢአቱን ቍርባን፣ የበደሉን ቍርባን ያስቀምጣሉ፤ ቦታው ቅዱስ ነውና። 14ካህናቱ አንድ ጊዜ ወደ ተቀደሰው ቦታ ከገቡ በኋላ፣ ያገለገሉበትን ልብስ ሳያወልቁ ወደ ውጩ አደባባይ መውጣት አይችሉም፤ የተቀደሰ ነውና፤ ወደ ሕዝቡ ቦታ ከመምጣታቸው በፊት ሌላውን ልብሳቸውን መልበስ አለባቸው።”

15በቤተ መቅደሱ ውስጥ ያለውን ስፍራ ለክቶ ከጨረሰ በኋላ፣ በምሥራቅ በር በኩል ወደ ውጩ አወጣኝ፤ በዙሪያው ያለውንም ስፍራ ሁሉ ለካ፤ 16በምሥራቅ ያለውንም በመለኪያው ዘንግ ለካ፤ አምስት መቶ ክንድ42፥16 ከሰብዐ ሊቃናት 17ን ይመ፤ ዕብራይስጡ ግን ዘንጎች ይለዋል፤ እንዲሁም 18 እና 19 ሆነ። 17ሰሜኑንም ለካ፤ በመለኪያው ዘንግ አምስት መቶ ክንድ42፥17 ሰብዐ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን ዘንጎች ይላል ሆነ። 18ደቡቡንም ለካ፤ በመለኪያው ዘንግ አምስት መቶ ክንድ ሆነ። 19ከዚያም ወደ ምዕራብ ጐን ዞሮ ለካ፤ በመለኪያው ዘንግ አምስት መቶ ክንድ ሆነ። 20ስለዚህ በአራቱም ማእዘን ለካው፤ የተቀደሰውን ስፍራ ከሌላው የሚለይ በዙሪያው ግንብ ነበረ፤ የግንቡም ርዝመት አምስት መቶ ክንድ ሲሆን፣ ወርዱ አምስት መቶ ክንድ ነበር።

Swedish Contemporary Bible

Hesekiel 42:1-20

Prästernas rum

1Han förde mig ut till den yttre förgården, norrut. Sedan förde han mig till byggnaden med rum mitt emot tempelgården och mitt emot tempelbyggnaden, norrut. 2Denna byggnad mot norr var 50 meter lång och 25 meter bred. 3Byggnaden låg mitt emot den inre förgårdens 10 meter breda plats och mitt emot den yttre förgårdens stengolv och var byggd i avsatser i tre våningar.42:3-6 Grundtexten är mycket svårtolkad och översättningen därmed osäker, delvis gjord med hjälp av Septuaginta och andra gamla översättningar (t.ex. längden av gången i v. 4, som enligt den masoretiska texten bara är en halv meter). 4En 5 meter bred och 50 meter lång inre gång gick längs rummen. Ingångarna låg mot norr. 5De övre rummen var smalare än de undre, därför att avsatsen längst nere och i mellanvåningen tog mer plats. 6Rummen låg i tre våningar och hade inga pelare, som i förgårdarna, därför var den översta våningens rum mindre än de nedersta och de mellersta våningarnas.

7Längs rummen gick en mur, mot yttre förgården, framför rummen. Den var 25 meter lång. 8Längden på raden av rum vid den yttre förgården var 25 meter, medan den vid tempelbyggnaden var 50 meter. 9Från öster fanns det en ingång till rummen längst ner, från den yttre förgården.

10På södra42:10 Egentligen östra; översättningen följer här Septuaginta. sidan av förgårdens mur, mitt emot templet och tempelgården, fanns också rum. 11Det fanns en gång framför dem. De var likadana som rummen i norr, hade samma längd och bredd, var likadant konstruerade och hade likadana utgångar. 12Dörrarna till rummen i söder låg i öster. Där fanns också en dörr i början av den väg som gick längs muren till ingången av rummen.

13Sedan sa han till mig: ”Dessa norra och södra rum mitt emot tempelgården är heliga rum. Där ska de präster som får vara nära Herren äta de högheliga offren. Där ska de förvara de högheliga offren, matoffret, syndoffret och skuldoffret, för platsen är helig. 14När prästerna går in på det heliga området, får de inte gå ut på den yttre förgården utan att ha lämnat kvar de kläder de bär i sin tjänstgöring, för de är heliga. De ska ta på sig andra kläder innan de går ut till det område som är för folket.”

15När han hade avslutat mätningarna av det inre tempelområdet tog han med mig ut genom porten i öster för att mäta området runt om. 16Han mätte med sin måttstock42:16 Se not till 40:5. den östra sidan, och den var 250 meter. 17Sedan mätte han med sin måttstock den norra sidan, som var 250 meter. 18Därefter mätte han med sin måttstock den södra sidan, som var 250 meter, 19och vände sig sedan västerut och mätte också den sidan, 250 meter med måttstocken. 20Så mätte han alla fyra sidorna. Den var omgiven av en mur som skilde det heliga från det som inte var heligt.