ሕዝቅኤል 41 – NASV & BDS

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 41:1-26

1ከዚያም ወደ መቅደሱ አገባኝ፤ ዐምዶቹንም ለካ፤ የዐምዶቹም ወርድ41፥1 አንድ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጅና ሰብዐ ሊቃናት እንዲሁ ሲሆኑ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች ግን …የድንኳኑ ወርድ ይላሉ በአንዱ በኩል ስድስት ክንድ፣ በሌላውም በኩል ስድስት ክንድ ነበር። 2የመግቢያውም በር ወርድ ዐሥር ክንድ ሲሆን፣ በግራና በቀኝ በኩል ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦች ወርድ አምስት ክንድ ነበር። ደግሞም የውስጡን መቅደስ ለካ፤ ርዝመቱ አርባ ክንድ፣ ወርዱም ሃያ ክንድ ነበር።

3ከዚያም ወደ ውስጥ ገባ፤ የመግቢያውን ዐምዶች ለካ፤ የእያንዳንዱም ወርድ ሁለት ክንድ ነበር። የመግቢያውም ወርድ ስድስት ክንድ ሲሆን፣ ግራና ቀኝ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦች ወርድ ደግሞ ሰባት ክንድ ነበር። 4እርሱም የውስጠኛውን መቅደስ ርዝመት ለካ፤ ሃያ ክንድ ነበር፤ ወርዱም የውጪውን ግድግዳ ጨምሮ ሃያ ክንድ ነበር፤ እርሱም፣ “ይህ ቅድስተ ቅዱሳን ነው” አለኝ።

5ከዚያም የቤተ መቅደሱን ግንብ ለካ፤ ውፍረቱ ስድስት ክንድ ነው፤ በቤተ መቅደሱ ግንብ ዙሪያ ግራና ቀኝ ያለው የእያንዳንዱ ክፍል ወርድ አራት ክንድ ነበር። 6ግራና ቀኝ ያሉት ክፍሎች፣ ባለ ሦስት ደርብ ናቸው፤ በእያንዳንዱም ደርብ ላይ ሠላሳ ክፍሎች ነበሩ፤ በግንቡም ዙሪያ ግራና ቀኝ ያሉትን እነዚህን ክፍሎች ደግፈው የሚይዙ ተሸካሚዎች ነበሩ፤ ሆኖም ተሸካሚዎቹ ወደ ቤተ መቅደሱ ግንብ ዘልቀው አልገቡም ነበር። 7በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ያሉት ክፍሎች ስፋት በየደርቡ እየጨመረ የሚሄድ ነው። በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ያለው ሕንጻ አሠራሩ ከታች ወደ ላይ እየሰፋ የሚሄድ በመሆኑ፣ ወደ ላይ በተሄደ ቍጥር የክፍሎቹ ስፋት እየጨመረ የሚሄድ ነው። በመካከለኛው ደርብ በኩል አድርጎ ከታች ወደ ላይ የተዘረጋም ደረጃ አለ። 8ቤተ መቅደሱ ዙሪያውን ከፍ ብሎ የተሠራ መሠረት ያለው መሆኑን አየሁ፤ ይህ ግራና ቀኝ ላሉት ክፍሎች መሠረት ሲሆን፣ ርዝመቱ ስድስት ክንድ ነው፤ ይህም የዘንጉ ቁመት ነበር። 9በውጭ በኩል ያለው የግራና የቀኙ ክፍሎች ግንብ ውፍረት አምስት ክንድ ነበር፤ ክፍቱ ቦታ በቤተ መቅደሱና 10በካህናቱ ክፍሎች መካከል ያለ ሲሆን፣ ስፋቱ በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ሃያ ክንድ ነበር። 11ከክፍቱ ቦታ ግራና ቀኝ ወዳሉ ክፍሎች የሚያስገቡ በሮች ነበሩ። አንዱ በሰሜን በኩል ሲሆን፣ ሌላው በር ደግሞ በደቡብ በኩል ነው። ክፍቱን ቦታ ዙሪያውን የሚያገናኘው መሠረት ስፋቱ አምስት ክንድ ነው።

12በምዕራብ በኩል ከቤተ መቅደሱ ግቢ ትይዩ የሆነው ሕንጻ ወርድ ሰባ ክንድ ነበር። የሕንጻው ግንብ ውፍረት ዙሪያውን አምስት ክንድ ሲሆን፣ ርዝመቱ ዘጠና ክንድ ነበር።

13ከዚያም ቤተ መቅደሱን ለካ፤ ርዝመቱ አንድ መቶ ክንድ ሲሆን፣ የቤተ መቅደሱ ግቢና ሕንጻ ከነግንቡ ደግሞ አንድ መቶ ክንድ ሆነ። 14በምሥራቅ በኩል የቤተ መቅደሱ ግቢ ስፋት፣ ከቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት ያለውን ስፍራ ጨምሮ አንድ መቶ ክንድ ነበር።

15ከዚያም ከቤተ መቅደሱ በስተ ጀርባ ከግቢው ትይዩ ያለውን ሕንጻ ለካ፤ ይህም በግራና በቀኝ ያሉትን መተላለፊያዎች የሚጨምር ሲሆን፣ ርዝመቱ አንድ መቶ ክንድ ነበር።

የውጩ መቅደስና የውስጡ መቅደስ ከአደባባዩ ትይዩ ያለው መተላለፊያ በረንዳ፣ 16እንዲሁም መድረኮቹና ጠበብ ያሉት መስኮቶች፣ በሦስቱም ዙሪያ ያሉት መተላለፊያዎች፣ ከመድረኩ በላይና ራሱ መድረኩም ጭምር ሁሉም በዕንጨት ተለብዶ ነበር። ወለሉ፣ እስከ መስኮቶቹ ያለው ግንብና መስኮቶቹ ተለብደዋል። 17ከውስጡ መቅደስ መግቢያ በላይ ያለው ውስጡና ውጩ እንዲሁም በውስጡ መቅደስና በውጩ መቅደስ መካከል ያለው ሁሉ ዙሪያውን 18ኪሩቤልና የዘንባባ ዛፍ ተቀርጸውበት ነበር፤ የዘንባባ ዛፎቹ የተቀረጹት በኪሩብና በኪሩብ መካከል ነበር። እያንዳንዱም ኪሩብ ሁለት ፊት ነበረው፤ 19የሰው ፊት ያለው ኪሩብ በአንድ በኩል ወዳለው ዘንባባ የዞረ ሲሆን፣ የአንበሳ ፊት ያለውም በሌላ በኩል ወዳለው ዘንባባ ዞሮ ነበር። ሁሉም በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ላይ ተቀርጸው ነበር። 20ከወለሉ አንሥቶ ከመግቢያው በላይ እስካለው ስፍራ ድረስ፣ የውስጡ መቅደስ የውጭ ግድግዳ ላይ ኪሩቤልና የዘንባባ ዛፍ ተቀርጿል።

21የውስጡ መቅደስ በር መቃን ባለ አራት ማእዘን ነበር፤ ከቅድስተ ቅዱሳኑም ፊት ለፊት ያለው በር እንዲሁ ባለ አራት ማእዘን ነበር። 22ሦስት ክንድ ቁመት፣ ሁለት ክንድ41፥22 ሰብዐ ሊቃናቱ እንዲሁ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን ርዝመቱ ሁለት ወርድ ይላል ወርድ፣ ሁለት ክንድ ርዝመት ያለው የዕንጨት መሠዊያ ነበር፤ ማእዘኖቹ፣ መሠረቱና41፥22 ሰብዐ ሊቃናቱ እንዲሁ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን ርዝመቱ ይላል ጐኖቹ ሁሉ ከዕንጨት የተሠሩ ነበሩ። ሰውየውም፣ “ይህች በእግዚአብሔር ፊት ያለች ገበታ ናት” አለኝ። 23የውስጡ መቅደስና ቅድስተ ቅዱሳኑ እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት በር አላቸው፤ 24እያንዳንዱ በር መካከሉ ላይ በመታጠፊያ የተያያዙ መዝጊያዎች አሉት። 25በግንቦቹ ላይ እንዳለው ሁሉ በውስጡ መቅደስ በሮችም ላይ ኪሩቤልና የዘንባባ ዛፎች ተቀርጸዋል፤ በመተላለፊያ በረንዳውም ፊት ለፊት የዕንጨት መዝጊያ ተንጠልጥሏል። 26በመተላለፊያ በረንዳውም ግራና ቀኝ ግንብ ላይ የዘንባባ ዛፍ ቅርጽ ያለባቸው ጠባብ መስኮቶች ነበሩ። ግራና ቀኝ ያሉት ክፍሎችም በደረጃው በኩል የሚሸፍን ጣሪያ ነበራቸው።

La Bible du Semeur

Ezéchiel 41:1-26

Dans le Temple

1Le personnage me fit ensuite entrer dans la grande salle du Temple et il en mesura les piliers : ils avaient six coudées d’épaisseur de chaque côté. 2La porte avait dix coudées de largeur et ses murs latéraux, de part et d’autre, cinq coudées. Il mesura la longueur de la grande salle : quarante coudées, et sa largeur : vingt coudées. 3Pénétrant à l’intérieur, il mesura les piliers de l’entrée : deux coudées, et l’entrée elle-même : six coudées, ses murs latéraux de chaque côté avaient sept coudées41.3 Ses murs latéraux… sept coudées: d’après l’ancienne version grecque (cf. 40.48 et note). Le texte hébreu traditionnel a : et la largeur de l’entrée était de sept coudées.. 4Il mesura la longueur de la pièce : vingt coudées, et autant de largeur face à la grande salle. Puis il me dit : Cette partie est le lieu très saint.

5Ensuite il mesura l’épaisseur du mur du Temple : six coudées, et la largeur de l’édifice latéral : quatre coudées sur tout le pourtour du Temple.

6Il y avait trois étages de trente salles qui étaient soutenues par un mur construit autour du Temple, de manière à ce que ces chambres s’y encastrent, sans être encastrées dans le mur même du Temple. 7A mesure que l’on montait d’un étage à l’autre, en tournant, les salles s’élargissaient aux dépens du mur tout autour du Temple : vers le haut de la maison, il y avait donc plus d’espace. On montait de l’étage inférieur à l’étage supérieur en passant par l’étage intermédiaire. 8Je vis aussi une terrasse surélevée tout autour de l’édifice, à la base des salles annexes, qui avait la longueur d’une règle, c’est-à-dire six coudées. 9L’épaisseur du mur extérieur des chambres latérales était de cinq coudées. L’espace libre entre les salles annexes du Temple 10et les salles des prêtres avait vingt coudées de large, tout autour de l’édifice. 11L’entrée des salles annexes donnait sur cet espace libre par une porte au nord et une au sud. Le passage avait cinq coudées de large tout autour. 12Du côté ouest, il y avait un bâtiment large de soixante-dix coudées attenant à l’espace libre ; sa muraille, longue de quatre-vingt-dix coudées, avait cinq coudées d’épaisseur sur tout le pourtour.

13Le personnage mesura le Temple ; longueur : cent coudées et même dimension pour l’espace libre, le bâtiment occidental et ses murailles. 14A l’est de ce bâtiment, la largeur de la façade arrière du Temple additionnée de l’espace libre était de cent coudées. 15Il mesura de même la longueur du bâtiment du côté de la cour arrière, y compris les galeries de chaque côté, et il trouva encore cent coudées.

La décoration intérieure

Dans le Temple, la grande salle, le portique donnant sur le parvis, 16les seuils, les fenêtres grillagées et les galeries du pourtour sur trois côtés, face au seuil41.16 sur trois côtés, face au seuil: hébreu obscur et traduction incertaine., étaient garnis d’un lambris de bois tout autour, jusqu’à la hauteur des fenêtres, et les fenêtres elles-mêmes étaient lambrissées 17jusqu’au-dessus de l’entrée et jusqu’au fond de la maison, et à l’extérieur sur tous les murs du pourtour ; à l’intérieur comme à l’extérieur, à intervalles réguliers 18on avait sculpté des chérubins et des palmiers : un palmier entre deux chérubins. Chaque chérubin avait deux faces : 19une face d’homme tournée vers l’un des palmiers et une face de lion tournée vers l’autre. Ces décorations se retrouvaient tout autour de la maison. 20Depuis le sol jusqu’au-dessus de la porte, il y avait des chérubins et des palmiers, et aussi sur les murs du Temple41.20 du Temple. Autre traduction : de la grande salle..

21Les encadrements des portes du Temple étaient constitués par des poteaux carrés. Devant le lieu saint41.21 Ezéchiel appelle « lieu saint » ou « sanctuaire » ce qu’on appelle généralement : « lieu très saint »., il y avait quelque chose qui ressemblait à 22un autel de bois haut de trois coudées et long de deux coudées. Ses coins, son socle et ses parois étaient en bois. Le personnage me dit : Voici la table qui est devant l’Eternel.

23La grande salle et le sanctuaire avaient chacun une double porte 24à deux battants pivotants. 25La porte de la grande salle était décorée de chérubins et de palmiers, comme les parois. A l’extérieur du portique, il y avait un auvent de bois. 26De chaque côté des fenêtres grillagées ainsi que sur les parois latérales du portique, sur celles des salles annexes du Temple et sur les auvents, on retrouvait les palmiers décoratifs.