ሕዝቅኤል 40 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 40:1-49

አዲሱ ቤተ መቅደስ

1በተሰደድን በሃያ አምስተኛው ዓመት፣ በዓመቱ መጀመሪያ፣ በዐሥረኛው ቀን፣ ከተማዪቱ በወደቀች በዐሥራ አራተኛው ዓመት፣ በዚያው ዕለት የእግዚአብሔር እጅ በላዬ ነበር፤ እርሱም ወደዚያ ወሰደኝ። 2በእግዚአብሔር ራእይ ወደ እስራኤል ምድር አመጣኝ፤ ከፍ ባለ ተራራ ላይ አኖረኝ፤ ከተራራውም በስተ ደቡብ፣ ከተማ የሚመስሉ ሕንጻዎች ነበሩ። 3ወደዚያ ወሰደኝ፤ እነሆ መልኩ ናስ የሚመስል ሰው አየሁ፤ እርሱም የሐር ገመድና መለኪያ ዘንግ በእጁ ይዞ በመግቢያው በር ላይ ቆሞ ነበር። 4ሰውየውም እንዲህ አለኝ፤ “የሰው ልጅ ሆይ፤ በዐይንህ እይ፤ በጆሮህ ስማ፤ የማሳይህንም ሁሉ ልብ ብለህ አስተውል፤ ወደዚህ የመጣኸው ለዚህ ነውና ያየኸውንም ሁሉ ለእስራኤል ቤት ንገር።”

ወደ ውጩ አደባባይ የሚያወጣው የምሥራቅ በር

5የቤተ መቅደሱን ዙሪያ ሙሉ በሙሉ የከበበ ቅጥር አየሁ፤ በሰውየውም እጅ ርዝመቱ ስድስት ክንድ የሆነ መለኪያ ዘንግ አየሁ፤ እያንዳንዱ ክንድ፣ አንድ ክንድ ከስንዝር ነበር፤ እርሱም ቅጥሩን ለካው፤ ስፋቱ አንድ መለኪያ ዘንግ ሲሆን፣ ቁመቱም እንዲሁ አንድ መለኪያ ዘንግ ነበር።

6ከዚያም በምሥራቅ ትይዩ ወዳለው በር መጣ፤ ደረጃዎቹን ወጥቶ የበሩን መግቢያ መድረክ ለካ፤ ቁመቱም አንድ ዘንግ ነበር።40፥6 ከሰብዓ ሊቃናት ጋር ተመሳሳይ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን የመጀመሪያው ጕበን ርዝመቱ አንድ ዘንግ ነበር ይላል። 7የዘብ ጠባቂ ቤቶች፣ ቁመታቸው አንድ መለኪያ ዘንግ፣ ወርዳቸውም አንድ መለኪያ ዘንግ ነበር፤ በቤቶቹም መካከል ያሉት ግንቦች ውፍረት አምስት ክንድ ነበር። ከቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት ባለው መተላለፊያ በረንዳ አጠገብ በውስጥ በኩል ያለው የበሩ መድረክ ወለል አንድ ዘንግ ነበር።

8ከዚያም የመግቢያውን በር መተላለፊያውን በረንዳ ለካ፤ 9ቁመቱ40፥8-9 በብዙ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች በሰብዓ ሊቃናት፣ በቩልጌትና በሱርስቱም እንዲሁ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች ግን በቤተ መቅደሱ ትይዩ ያለ፣ የመግቢያ በር ነው፤ አንድ ክንድ ነበር 9 ከዚያም የመግቢያ በሩን መተላለፊያ በረንዳ ለካው ይላሉ። ስምንት ክንድ፣ የዐምዶቹም ውፍረት ሁለት ክንድ ነበር። የመግቢያው በር መተላለፊያ በረንዳ፣ ከቤተ መቅደሱ ትይዩ ነው።

10በምሥራቁ በር ግራና ቀኝ መጠናቸው እኩል የሆነ ሦስት ሦስት የዘብ ቤቶች ነበሩ፤ በመካከላቸው ወጣ ወጣ ብለው የሚታዩትም ግንቦች ተመሳሳይና እኩል ነበሩ። 11ከዚያም የበሩን ስፋት ለካ፤ ወርዱ ዐሥር ክንድ፣ ርዝመቱም ዐሥራ ሦስት ክንድ ነበር። 12በእያንዳንዱ ዘብ ቤት ፊት ለፊት ከፍታው አንድ ክንድ የሆነ መከለያ የግንብ ዐጥር አለ፤ የዘብ ቤቶቹም ስፋት እኩል በኩል ስድስት ክንድ ነበር። 13ከዚያም ከዘብ ቤቱ የኋላ ግድግዳ ጀምሮ እስከ ሌላው ጫፍ ድረስ ያለውን የመግቢያ በር ለካ፤ ከአንዱ መከለያ ግድግዳ እስከ ሌላው መከለያ ግድግዳ ያለው ርቀት ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 14በመግቢያው በር ዙሪያ ባሉት ወጣ ወጣ ባሉት ግንቦች ሁሉ ፊት ለፊት ያለውን ቦታ ለካ፤ ስድሳ ክንድም ነበር። የተለካውም ከአደባባዩ40፥14 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ወጣ ያለ ግንብ ይለዋል። ፊት ለፊት እስካለው መተላለፊያ በረንዳ40፥14 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም። ድረስ ነበር። 15ከበሩ መግቢያ እስከ መተላለፊያ በረንዳው መጨረሻ ድረስ ያለው ርቀት አምሳ ክንድ ነበር። 16ክፍሎቹ እንደ መተላለፊያ በረንዳዎቹ ከግራና ከቀኝ በኩል ትንንሽ መስኮቶች አሏቸው። በዙሪያው ያሉ መስኮቶች በመግቢያው በር ፊት ለፊት የነበሩ ሲሆን፣ በእያንዳንዱ ክፍል ግራና ቀኝ ግድግዳ ላይ ደግሞ የዘንባባ ዛፍ ተቀርጾበታል።

የውጩ አደባባይ

17ከዚያም ወደ ውጩ አደባባይ አመጣኝ፤ እዚያም በአደባባዩ ዙሪያ የተሠሩ ክፍሎችና ድንጋይ የተነጠፈበት መመላለሻ አየሁ፤ በመመላለሻውም ዙሪያ ሠላሳ ክፍሎች ነበሩ። 18የታችኛው ንጣፍ ወለል ከመግቢያው በር ጋር ተያይዞ የተሠራ ሲሆን፣ ስፋቱ እንደ በሮቹ ርዝመት መጠን ነበር። 19ከዚያም ከታችኛው መግቢያ በር ፊት ጀምሮ እስከ ውስጠኛው አደባባይ ፊት ድረስ ያለውን ርቀት ለካ፤ በምሥራቅም ሆነ በሰሜን በኩል ያለው ርቀት አንድ መቶ ክንድ ነበር።

የሰሜኑ በር

20ከዚያም በሰሜን ትይዩ ያለውን፣ ወደ ውጩ አደባባይ የሚያመራውን በር ርዝመትና ወርድ ለካ። 21እንደ መጀመሪያው በር ሁሉ ይኸኛውም በየጐኑ ያሉት ሦስት ሦስት የዘብ ቤቶች፣ በየመካከሉ ወጣ ወጣ ያሉ ግንቦችና መተላለፊያ በረንዳዎቹ መጠናቸው እኩል ነበር። ርዝመቱ አምሳ ክንድ፣ ወርዱም ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 22መስኮቶቹ፣ መተላለፊያ በረንዳዎቹና የዘንባባ ዛፍ ቅርጾቹ ልካቸው በምሥራቁ በር ካሉት ጋር ተመሳሳይ ነበር። ወደዚያ የሚያመሩ ሰባት ደረጃዎች አሉ፤ መተላለፊያ በረንዳዎቹም ከእነርሱ ጋር ትይዩ ነበር። 23ልክ በምሥራቅ በኩል እንዳለው ሁሉ፣ ከሰሜኑ በር ጋር ትይዩ የሆነ ወደ ውስጠኛው አደባባይ የሚያመራ በር አለ። ከአንዱ በር እስከ ሌላኛው በር ያለውን ለካው፤ ይህም አንድ መቶ ክንድ ነበር።

የደቡቡ በር

24ከዚያም ወደ ደቡብ አቅጣጫ መራኝ፤ እዚያም ፊቱን ወደ ደቡብ ያደረገ በር አየሁ፤ እርሱም የውስጠኛውን ግድግዳና መተላለፊያ በረንዳውን ለካ፤ የእነዚህም መጠን እንደ ሌሎቹ በሮች ነበር። 25የመግቢያው በርና መተላለፊያ በረንዳው እንደ ሌሎቹ ሁሉ በዙሪያው ጠባብ መስኮቶች ነበሩት፤ ርዝመቱ አምሳ ክንድ፤ ወርዱም ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 26ከመተላለፊያ በረንዳው ትይዩ የሆኑ ሰባት ደረጃዎች ወደ መግቢያው በር ያመራሉ፤ ወጣ ወጣ ብለው በሚታዩ ግድግዳዎችም ላይ የዘንባባ ቅርጽ አለ። 27ውስጠኛው አደባባይ ደግሞ ከደቡብ ጋር ትይዩ የሆነ በር አለው፤ እርሱም ከዚህ በር አንሥቶ በደቡብ አቅጣጫ እስካለው እስከ ውጭው በር ድረስ ለካው፤ ይህም አንድ መቶ ክንድ ሆነ።

ወደ ውስጠኛው አደባባይ የሚያስገቡ በሮች

28ከዚያም በደቡብ በር በኩል ወደ ውስጠኛው አደባባይ አመጣኝ፤ የደቡብንም በር ለካው፤ መጠኑም እንደ ሌሎቹ በሮች ነበር። 29የዘብ ቤቶቹ፣ በየመካከሉ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦችና መተላለፊያ በረንዳዎቹ መጠናቸው ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር። መግቢያው በርና መተላለፊያ በረንዳዎቹ በዙሪያቸው መስኮቶች ነበሯቸው። ርዝመቱ አምሳ ክንድ ወርዱም ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 30በውስጠኛው አደባባይ ዙሪያ ያሉት የመግቢያው በር መተላለፊያ በረንዳዎቹ ርዝመት ሃያ አምስት ክንድ ሲሆን፣ ወርዳቸው ደግሞ አምስት ክንድ ነበር። 31መተላለፊያ በረንዳው ከውጭው አደባባይ ጋር ትይዩ ነው፤ የዘንባባ ዛፎች በዐምዶቹ ላይ ተቀርጸዋል፤ እስከ መግቢያው ድረስም ስምንት ደረጃዎች ነበሩት።

32ከዚያም በምሥራቅ በኩል ወደ ውስጠኛው አደባባይ አመጣኝ፤ መግቢያ በሩንም ለካው፤ መጠኑም ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር። 33የዘብ ቤቶቹ፣ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦችና መተላለፊያ በረንዳዎቹ መጠናቸው ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር፤ መግቢያው በርና መተላለፊያ በረንዳው ዙሪያውን መስኮቶች ነበሩት፤ የዚህም ርዝመቱ አምሳ ክንድ፣ ወርዱ ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 34መተላለፊያ በረንዳው ከውጩ አደባባይ ትይዩ ነው፤ በዐምዶቹ ላይ የዘንባባ ዛፍ ተቀርጿል፤ እስከ መግቢያ ድረስም ስምንት ደረጃዎች ነበሩት።

35ከዚያም ወደ ሰሜን በር አመጣኝ፤ ለካውም፤ መጠኑም ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር። 36የዘብ ቤቶቹ፣ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦቹና መተላለፊያ በረንዳው መጠናቸው ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር፤ በዙሪያውም መስኮቶች ነበሩት። የዚህም ርዝመቱ አምሳ ክንድ ወርዱም ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 37መተላለፊያ በረንዳው40፥37 ሰብዓ ሊቃናቱም (በተጨማሪ 31 እና 34 ይመ) እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን መቃኖች ይላል። ከውጩ አደባባይ ትይዩ ነው፤ በዐምዶቹም ላይ የዘንባባ ዛፍ ተቀርጿል፤ እስከ መግቢያው ድረስም ስምንት ደረጃዎች ነበሩት።

መሥዋዕት የሚዘጋጅባቸው ክፍሎች

38በእያንዳንዱ የውስጥ መግቢያ በር መተላለፊያ በረንዳ አጠገብ የሚቃጠል መሥዋዕት የሚታጠብበት በር ያለው ክፍል አለ። 39በመግቢያው በር ላይ ባለው መተላለፊያ በረንዳው ሥር በግራና በቀኝ የሚቃጠል መሥዋዕት፣ የኀጢአትና የበደል መሥዋዕት የሚታረዱበት ሁለት ሁለት ጠረጴዛዎች አሉ። 40ከመግቢያው በር ላይ ባለው መተላለፊያ በረንዳ በስተ ውጭው ግንብ ወደ ሰሜን በር መግቢያ ላይ ባሉት ደረጃዎች አጠገብ ከግራና ከቀኝ ሁለት ሁለት ጠረጴዛዎች ይገኛሉ። 41ስለዚህ በአንዱ በር በኩል አራት፣ በሌላውም በኩል አራት ጠረጴዛዎች፤ መሥዋዕቱ የሚታረድባቸው በድምሩ ስምንት ጠረጴዛዎች አሉ ማለት ነው። 42ለሚቃጠለው መሥዋዕት መገልገያ የሆኑ፣ ከተጠረበ ድንጋይ የተሠሩ አራት ጠረጴዛዎች ነበሩ፤ የእያንዳንዳቸው ርዝመት፣ ወርድና ቁመት አንድ ክንድ ተኩል ነበር፤ በእነዚህም ላይ ለሚቃጠለው መሥዋዕትና ለሌላውም መሥዋዕት ማረጃ የሚሆኑ መሣሪያዎች ይቀመጡባቸው ነበር። 43እንዲሁም አንዳንድ ስንዝር የሚሆኑ ሁለት ጣት ያላቸው ሜንጦዎች በግንቡ ዙሪያ ተንጠልጥለው ነበር፤ ጠረጴዛዎቹም የመሥዋዕቱ ሥጋ ማስቀመጫ ነበሩ።

ለካህናት የተመደቡ ክፍሎች

44በውስጠኛው አደባባይ፣ ከውስጠኛው በር ውጭ፣ ሁለት ክፍሎች ነበሩ፤ አንዱ40፥44 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን የመዘመራን ክፍሎች ነበሩ ይላል። በደቡብ40፥44 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን በምሥራቅ ይላል። ትይዩ በሰሜን በር በኩል ሲሆን፣ ሌላው በሰሜን ትይዩ በደቡብ በር በኩል ነበር። 45እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “በደቡብ ትይዩ ያለው ክፍል በቤተ መቅደስ ውስጥ ለሚያገለግሉ ካህናት ሲሆን፣ 46በሰሜን ትይዩ ያለው ክፍል ደግሞ በመሠዊያው ላይ ለሚያገለግሉ ካህናት ነው። እነዚህም የሳዶቅ ልጆች ሲሆኑ፣ በእግዚአብሔር ፊት ቀርበው ማገልገል የሚችሉ ሌዋውያን እነርሱ ብቻ ናቸው።”

47ከዚያም አደባባዩን ለካው፤ ርዝመቱ አንድ መቶ ክንድ፣ ወርዱ መቶ ክንድ እኩል በእኩል ባለ አራት ማእዘን ነበር። መሠዊያውም በቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት ነበር።

ቤተ መቅደሱ

48ወደ ቤተ መቅደሱም መተላለፊያ በረንዳ አመጣኝ፤ የመተላለፊያ በረንዳዎቹን ዐምዶች ለካ፤ በአንዱ በኩል አምስት ክንድ በሌላውም እንዲሁ አምስት ክንድ ነበር። የመግቢያው በር ርዝመት ዐሥራ አራት ክንድ ሲሆን፣ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦች ስፋት በአንዱ በኩል ሦስት ክንድ፣ በሌላውም እንዲሁ ሦስት ክንድ ነበሩ።40፥48 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦች መግቢያ… ነበሩ ይላል። 49የመተላለፊያው በረንዳ ርዝመት ሃያ ክንድ፣ ከፊት እስከ ኋላ ያለውም ወርድ ዐሥራ ሁለት40፥49 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ዐሥራ አንድ ይላል። ክንድ ነበር። ወደ ቤተ መቅደሱም የሚያደርሱ ዐሥር ደረጃዎች የነበሩ ሲሆን፣ በየዐምዱም ጐንና ጐን ምሰሶዎች ነበሩ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以西結書 40:1-49

新聖殿的異象

1在我們被擄的第二十五年,就是耶路撒冷淪陷的第十四年一月十日,耶和華的靈降在我身上。 2在異象中上帝把我帶到以色列的一座高山上,山的南面彷彿有一座城。 3祂把我帶到那裡。城的入口站著一個面色如銅的人,手中拿著一條麻繩和一根量竿。 4那人對我說:「人子啊,你要留心用眼看,專心用耳聽,注意我指示你的一切,因為我帶你來這裡正是為了要指示你。你要把所見到的一切告訴以色列人。」

外院的門

5我看見殿的四周有牆,那人拿了一根三米長的量竿測量這牆,量出牆厚一竿,高一竿。

6然後,他帶我到殿的東門,走上石階,來到門口。他量了門洞,寬一竿。 7門內有守衛室,長度和寬度都是一竿。室與室之間相距二點二米,通往聖殿的內門洞寬一竿, 8通往聖殿的門廊寬度也是一竿, 9連牆柱在內共四點二米寬,牆柱寬一點零五米。 10東門內共有六間守衛室,每邊三間,大小面積都是一樣,兩邊的牆尺寸也相同。 11通道盡頭有一道門廊,寬五米,長六點五米。 12兩邊守衛室前面的矮牆高五十釐米,守衛室都是三米寬的正方形。 13他又量門廊的寬度,即這邊守衛室的屋頂到對面守衛室的屋頂,是十二點五米。 14他從門口的牆量到外院的牆柱,是三十米。 15由門口到通道盡頭的內廊共二十五米, 16守衛室、牆柱上和門廊周圍都有格子窗,牆柱上刻著棕樹。

外院

17他帶我到外院,外院靠牆的四周是鋪石地,上面共有三十間廂房。 18鋪石地在門口的兩邊,比內院低,寬度與入口的長度一樣。 19他從外院的內門口量到內院的門口,距離是五十米。

北門

20他又量了外院的北門, 21通道兩邊各有三間守衛室,牆和廊子長度和寬度跟東門一樣,分別是二十五米和十二點五米。 22它的窗戶、門廊、牆柱上雕刻的棕樹都和東門的尺寸相同。登上七級石階便到達門口,通道的盡頭是門廊。 23內院的北門與外院的北門相對,正如它的東門和外院的東門相對,門與門之間的距離是五十米。

南門

24他又帶我到南門,量了牆柱和門廊,都與其他門的尺寸相同, 25通道與門廊四周的窗戶也和其他的門一樣,通道長二十五米,寬十二點五米。 26登上七級石階便到門廊,兩邊的牆柱也同樣刻著棕樹。 27內院也有南門,與外院南門之間的距離是五十米。

內院的門

28他帶我從南門走進內院,量了南門,跟其他門的尺寸一樣。 29守衛室、牆柱和門廊都和其他的尺寸一樣,通道與門廊四周有窗戶,通道長二十五米,寬十二點五米。 30內院周圍的門廊都是長十二點五米,寬二點五米。 31這些門廊靠外院,兩邊的牆柱刻著棕樹,上去的石階共有八級。

32他又帶我從東門進入內院,量了東門,跟其他門的尺寸一樣, 33守衛室、牆柱、門廊和其他門的尺寸一樣,通道與門廊的四周也有窗戶,通道長二十五米,寬十二點五米。 34門廊靠外院,兩邊的牆柱刻著棕樹,那裡的石階共有八級。

35他又帶我到北門,量了北門,跟其他門的尺寸一樣。 36守衛室、牆柱、門廊和其他門的尺寸一樣,通道長二十五米,寬十二點五米,四周有窗戶。 37門廊靠外院,兩邊的牆柱刻著棕樹,那裡的石階共有八級。

廂房

38門口的牆柱旁邊有一個房間,供祭司洗燔祭牲。 39門廊兩邊各有兩張用來屠宰燔祭牲、贖罪祭牲和贖過祭牲的桌子。 40內院北門的兩邊各有兩張桌子, 41即裡外各有四張桌子,共八張,供祭司屠宰祭牲之用。 42另有四張用石頭鑿成的桌子用來預備燔祭牲,屠宰燔祭牲及其他祭牲的器具都放在桌上。桌子長寬各七十五釐米,高五十釐米。 43廊內四周掛著七點五釐米長的雙鉤。桌上放著祭肉。

44在內院有歌樂手用的廂房,一間向南,在北門旁,一間向北,在南門旁。 45他對我說:「向南的廂房是給殿內供職的祭司用的, 46向北的廂房是給壇前供職的祭司用的。他們都是撒督的子孫,利未的後裔,在耶和華面前專職事奉。」 47他量了殿前的院子,是五十米寬的正方形,祭壇在殿的前面。

聖殿

48他帶我來到殿前通往聖所的門廊,量了兩旁的牆柱,各二點五米寬,門兩邊的牆一點五米厚, 49門廊長十米,寬四點九米。上門廊靠近牆柱的石級兩旁各有一根柱子。