በጎግ ላይ የተነገረ ትንቢት
1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን በማጎግ ምድር በሚገኘው፣ በሞሳሕና በቶቤል ዋና አለቃ38፥2 ወይም የሮሽ አለቃ በጎግ ላይ አድርግ፤ በእርሱ ላይ ትንቢት ተናገር፤ 3እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የሞሳሕና የቶቤል ዋና አለቃ38፥3 ወይም የሮሽ አለቃ ጎግ ጎግ ሆይ፤ ተነሥቼብሃለሁ። 4ወደ ኋላ እመልስሃለሁ፤ መንጋጋህ ውስጥ መንጠቆ አስገብቼ ከመላው ሰራዊትህ ጋር፣ ፈረሶችህን፣ ፈረሰኞችህን ከነሙሉ ትጥቃቸው፣ ትልቅና ትንሽ ሰይፍ የያዙትን ሁሉ፣ ሰይፋቸውንም የወለወሉትን ሁሉ አስወጣለሁ። 5ጋሻ የያዙና የራስ ቍር የደፉት ሁሉ፣ ፋርስ፣ ኢትዮጵያና ፉጥ ከእነርሱ ጋር ይሆናሉ። 6ደግሞም ጎሜርን ከወታደሮቹ ጋር፣ ራቅ ካለው ሰሜንም የቴርጋማን ቤት ከወታደሮቹ ሁሉ ጋር ብዙ ሕዝቦችን ከአንተ ጋር አስወጣለሁ።”
7“ ‘አንተና በዙሪያህ የተሰበሰቡት ሁሉ ተነሡ፤ ተዘጋጁ፤ አንተም መሪያቸው ሁን። 8ከብዙ ቀን በኋላ ለጦርነት ትጠራለህ። በኋለኛው ዘመንም ከጦርነት ያገገመችውን፣ ሕዝቧ ከአያሌ አሕዛብ መካከል ወጥቶ የተሰበሰበውን፣ ለብዙ ጊዜ ባድማ በነበረው በእስራኤል ተራሮች ላይ የሰፈረውን ወገን ትወርራለህ። ከሕዝቦች መካከል ወጥተው፣ አሁን ሁሉም በሰላም ይኖራሉ። 9አንተና ወታደሮችህ ሁሉ፣ ከአንተም ጋር ያሉት ብዙ ሕዝቦች እንደ ማዕበል ትወጣላችሁ፤ ምድርን እንደሚሸፍን ደመናም ትሆናላችሁ።
10“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በዚያ ቀን ሐሳብ ወደ አእምሮህ ይመጣል፤ ክፋትንም ታውጠነጥናለህ። 11እንዲህም ትላለህ፤ “ቅጥር የሌላቸውን መንደሮች ምድር እወራለሁ፤ ሁሉም ያለ ቅጥር፣ ያለ በርና ያለ ብረት መወርወሪያ የሚኖረውን፣ ሰላማዊና ያለ ሥጋት የተቀመጠውን ሕዝብ እወጋለሁ፤ 12እዘርፋለሁ፤ እነጥቃለሁ፤ እንዲሁም ከአሕዛብ ተሰባስቦ እንደ ገና በሰፈረው፣ በከብትና በሸቀጥ በከበረው፣ በምድሪቱም መካከል በሚኖረው ሕዝብ ላይ እጄን አነሣለሁ።” 13ሳባና ድዳን፣ የተርሴስ ነጋዴዎችና መንደሮቿም ሁሉ38፥13 ወይም ጠንካራ መንደሮቿ እንዲህ ይሉሃል፤ “ልትዘርፍ መጣህን? ሰራዊትህን ያሰባሰብኸው ለመበዝበዝ፣ ወርቅና ብሩን አጋብሶ ለመሄድ፣ ከብቱንና ሸቀጡን ለመውሰድ፣ ብዙ ምርኮ ይዞ ለመመለስ ነውን?” ’
14“ስለዚህ የሰው ልጅ ሆይ፤ ትንቢት ተናገር፤ ጎግንም እንዲህ በለው፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “በዚያ ቀን ሕዝቤ እስራኤል በሰላም መቀመጡን ዐውቀህ አትንቀሳቀስምን? 15በስተ ሰሜን ርቆ ከሚገኘው ቦታ ትመጣለህ፤ አንተና ከአንተም ጋር ብዙ ሕዝቦች፣ እጅግ ታላቅ ኀያል ሰራዊትም በፈረሶች ላይ ሆናችሁ ትመጣላችሁ። 16ምድርን እንደሚሸፍን ደመና ሆነህ በሕዝቤ በእስራኤል ላይ ትወጣለህ። ጎግ ሆይ፤ በፊታቸው ቅድስናዬን ስገልጥ ሕዝቦች እኔን ያውቁ ዘንድ በኋለኛው ዘመን በምድሬ ላይ አመጣሃለሁ።”
17“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “በቀደመው ዘመን በባሪያዎቼ በእስራኤል ነቢያት ስለ እርሱ የተናገርሁለት ያ ሰው አንተ አይደለህምን? በዚያን ወቅት አንተን በእነርሱ ላይ እንደማመጣባቸው ለብዙ ዓመታት ትንቢት ተናገሩ።” 18በዚያን ጊዜ እንዲህ ይሆናል፤ “ጎግ የእስራኤልን ምድር ሲወጋ፣ ብርቱ ቍጣዬ ይነሣሣል፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። 19በዚያን ጊዜ በቅናቴና በሚያስፈራው ቍጣዬ በእስራኤል ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ይሆናል ብዬ ተናግሬአለሁ። 20የባሕር ዓሦች፣ የሰማይ ወፎች፣ የምድር አራዊት፣ በምድር ላይ የሚሳብ ማንኛውም ፍጡር፣ እንዲሁም በምድር ላይ የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ፣ በፊቴ ይንቀጠቀጣሉ፤ ተራሮች ይገለባበጣሉ፤ ገደሎች ይናዳሉ፤ 21በተራሮቼም ሁሉ በጎግ ላይ ሰይፍ እጠራለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ የእያንዳንዱም ሰው ሰይፍ በወንድሙ ላይ ያርፋል። 22በቸነፈርና በደም መፋሰስ እፈርድበታለሁ፤ የዝናብ ዶፍ፣ የበረዶ ድንጋይ፣ የሚያቃጥል ድኝ፣ በእርሱና በወታደሮቹ፣ ከእርሱም ጋር ባሉት ሕዝቦች ላይ አወርዳለሁ። 23በዚህም ታላቅነቴንና ቅድስናዬን አሳያለሁ፤ በብዙ ሕዝቦች ፊት ራሴን አሳውቃለሁ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።” ’
پيشگويی بر ضد جوج
1-3اين پيغام نيز از جانب خداوند به من رسيد:
«ای انسان خاكی، رو به سرزمين ماجوج كه در سمت شمال است بايست و بر ضد جوج، پادشاه ماشک و توبال پيشگويی كن. به او بگو كه خداوند میفرمايد: من بر ضد تو هستم. 4قلاب در چانهات میگذارم و تو را به سوی هلاكت میكشم. سربازان پياده و سواران مسلح تو بسيج شده، سپاه بسيار بزرگ و نيرومندی تشكيل خواهند داد. 5پارس، كوش، و فوط هم با تمام سلاحهای خود به تو خواهند پيوست. 6تمام لشكر سرزمين جومر و توجرمه از شمال، و نيز بسياری از قومهای ديگر، به تو ملحق خواهند شد. 7ای جوج، تو رهبر آنها هستی، پس آماده شو و تدارک جنگ ببين!
8«پس از يک مدت طولانی از تو خواسته خواهد شد كه نيروهای خود را بسيج كنی. تو به سرزمين اسرائيل حمله خواهی كرد، سرزمينی كه مردم آن از اسارت سرزمینهای مختلف بازگشته و در سرزمين خود در امنيت ساكن شدهاند؛ 9ولی تو و تمام همپيمانانت سپاهی بزرگ تشكيل خواهيد داد و مثل طوفانی سهمگين بر آنها فرود خواهيد آمد و مانند ابری سرزمين اسرائيل را خواهيد پوشاند.»
10خداوند میفرمايد: «در آن هنگام تو نقشههای پليدی در سر خواهی پروراند؛ 11و خواهی گفت: ”اسرائيل يک مملكت بیدفاع است و شهرهايش حصار ندارند! به جنگ آن میروم و اين قوم را كه در كمال امنيت و اطمينان زندگی میكنند، از بين میبرم! 12به آن شهرهايی كه زمانی خراب بودند، ولی اينک آباد گشته و از مردمی پر شدهاند كه از سرزمينهای ديگر بازگشتهاند، حمله میكنم و غنايم فراوان به دست میآورم و بسياری را اسير میكنم. زيرا اكنون اسرائيل گاو و گوسفند و ثروت بسيار دارد و مركز تجارت دنياست.“
13«مردم سبا و ددان، و تجار ترشيش به تو خواهند گفت: ”آيا با سپاه خود آمدهای تا طلا و نقره و اموال ايشان را غارت كنی و حيواناتشان را با خود ببری؟“»
14خداوند به جوج میفرمايد: «زمانی كه قوم من در مملكت خود در امنيت زندگی كنند، تو بر میخيزی و 15-16با سپاه عظيم خود از شمال میآيی و مثل ابر زمين را میپوشانی. اين، در آيندهٔ دور اتفاق خواهد افتاد. من تو را به جنگ سرزمين خود میآورم، ولی بعد در برابر چشمان همه قومها تو را از ميان برمیدارم تا به همهٔ آنها قدوسيت خود را نشان دهم و تا آنها بدانند كه من خدا هستم.»
17خداوند میفرمايد: «تو همانی كه مدتها پيش توسط خدمتگزارانم يعنی انبيای اسرائيل در بارهات پيشگويی كرده، گفتم كه بعد از آنكه سالهای بسيار بگذرد، تو را به جنگ قوم خود خواهم آورد. 18اما وقتی برای خراب كردن مملكت اسرائيل بيايی، خشم من افروخته خواهد شد. 19من با غيرت و غضب گفتهام كه در آن روز در اسرائيل زلزلهٔ مهيبی رخ خواهد داد. 20و در حضور من تمام حيوانات و انسانها خواهند لرزيد. صخرهها تكان خواهند خورد و حصارها فرو خواهند ريخت. 21من كه خداوند هستم میگويم تو را ای جوج، به هر نوع ترسی گرفتار خواهم ساخت و سربازان تو به جان هم افتاده، يكديگر را خواهند كشت! 22من با شمشير، مرض، طوفانهای سهمگين و سيلآسا، تگرگ درشت و آتش و گوگرد با تو و با تمام سربازان و همپيمانانت خواهم جنگيد. 23به اين طريق عظمت و قدوسيت خويش را به همهٔ قومهای جهان نشان خواهم داد و آنها خواهند دانست كه من خداوند هستم.»