ሕዝቅኤል 34 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 34:1-31

እረኞችና በጎች

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ በእስራኤል እረኞች ላይ ትንቢት ተናገር፤ ትንቢት ተናገር፤ እንዲህም በላቸው፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ራሳቸውን ብቻ ለሚንከባከቡ ለእስራኤል እረኞች ወዮላቸው! እረኞች መንጋውን ማሰማራት አልነበረባቸውምን? 3ጮማውን ትበላላችሁ፤ ከጠጕሩ የተሠራውን ሱፍ ትለብሳላችሁ፤ የሰባውን ዐረዳችሁ፤ ነገር ግን መንጋውን አትንከባከቡትም። 4ደካማውን አላበረታችሁትም፤ በሽተኛውን አልፈወሳችሁትም፤ የተጐዳውንም አልጠገናችሁትም። የባዘኑትን አልመለሳችሁም፤ የጠፉትንም አልፈለጋችሁም፤ በግፍና በጭካኔ ገዛችኋቸው። 5ስለዚህ እረኛ የለምና ተበተኑ፤ በመበተናቸውም ለአራዊቱ ሁሉ መብል ሆኑ። 6በጎቼ በየተራራው ሁሉና በየኰረብታው ላይ ተንከራተቱ። በምድር ሁሉ ተበተኑ፤ የፈለጋቸውም፤ የፈቀዳቸውም የለም።

7“ ‘ስለዚህ እናንት እረኞች፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ 8በሕያውነቴ እምላለሁ፣ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ እረኞቼ መንጋዬን ስላልፈለጉ፣ ከመንጋዬም ይልቅ ራሳቸውን ስለ ተንከባከቡ፣ መንጋዬ እረኛ ዐጥቶ ለንጥቂያ ተዳርጓል፤ ለአራዊትም ሁሉ መብል ሆኗል። 9ስለዚህ እረኞች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ 10ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ እኔ በእረኞች ላይ ተነሥቻለሁ፤ ስለ መንጋዬ እጠይቃቸዋለሁ፤ ከእንግዲህ እረኞች ራሳቸውን መመገብ እንዳይችሉ፣ መንጋዬን እንዳያሰማሩ አደርጋለሁ። መንጋዬን ከአፋቸው አስጥላለሁ፤ ከእንግዲህም ምግብ አይሆናቸውም።

11“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ እኔ ራሴ በጎቼን እፈልጋቸዋለሁ፤ እጠብቃቸዋለሁም። 12እረኛ ከመንጋው ጋር ሳለ፣ የተበተኑበትን በጎች እንደሚፈልግ ሁሉ፣ እኔም በጎቼን እፈልጋለሁ። በደመናና በጨለማ ቀን ከተበተኑበት ስፍራ ሁሉ አድናቸዋለሁ። 13ከአሕዛብ መካከል አወጣቸዋለሁ፤ ከየአገሮቹ እሰበስባቸዋለሁ፤ ወደ ገዛ ምድራቸውም አመጣቸዋለሁ። በእስራኤል ተራሮች፣ በየወንዙ ዳርና፣ በምድሪቱ መኖሪያዎች ሁሉ እንዲሰማሩ አደርጋለሁ። 14በመልካሙ ስፍራ አሰማራቸዋለሁ፤ የእስራኤል ተራሮች ከፍታም የግጦሽ መሬት ይሆናቸዋል። በመልካሙ ግጦሽ መሬት ላይ ይተኛሉ፤ እዚያም በእስራኤል ተራሮች ለምለም መስክ ላይ ይመገባሉ። 15እኔ ራሴ በጎቼን አሰማራለሁ፤ አስመስጋቸዋለሁም። ይላል ጌታ እግዚአብሔር16የጠፉትን እፈልጋለሁ፤ የባዘኑትንም እመልሳለሁ። የተጐዱትን እጠግናለሁ፤ የደከሙትንም አበረታለሁ፤ የወፈረውንና የበረታውን ግን አጠፋለሁ። መንጋውን በፍትሕ እጠብቃለሁ።

17“ ‘መንጋዬ ስለ ሆናችሁት ስለ እናንተ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በበግና በበግ መካከል፣ በአውራ በግና በአውራ ፍየል መካከል እፈርዳለሁ። 18በለምለሙ መስክ ላይ መመገቡ አይበቃችሁምን? የተረፈውን መሰማሪያችሁን ደግሞ በእግራችሁ መረጋገጥ ይገባችኋልን? ንጹሕ ውሃ መጠጣቱ አይበቃችሁምን? የተረፈውንስ በእግራችሁ ማደፍረስ ይገባችኋልን? 19መንጋዬ የረጋገጣችሁትን መመገብና በእግራችሁ ያደፈረሳችሁትን መጠጣት ይገባዋልን?

20“ ‘ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላቸዋል፤ “እነሆ እኔ ራሴ በሰባው በግና በከሳው በግ መካከል እፈርዳለሁ። 21ደካሞቹን በጎች በጐናችሁና በትከሻችሁ ስለምትገፈትሩ፣ እስኪባረሩም ድረስ በቀንዳችሁ ስለምትወጓቸው፣ 22እኔ መንጋዬን አድናለሁ፤ ከእንግዲህ ለንጥቂያ አይዳረጉም፤ በአንዱ በግና በሌላውም በግ መካከል እፈርዳለሁ። 23በእነርሱ ላይ አንድ እረኛ፣ ባሪያዬን ዳዊትን አቆማለሁ፤ እርሱም ያሰማራቸዋል፤ እረኛቸውም ይሆናል። 24እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው እሆናለሁ፤ ባሪያዬ ዳዊትም በመካከላቸው ገዥ ይሆናል፤ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ።”

25“ ‘ከእነርሱ ጋር የሰላም ቃል ኪዳን እገባለሁ፤ ከዚያም ምድሪቱን ከዱር አራዊት ነጻ አደርጋለሁ፤ እነርሱም በምድረ በዳ ይኖራሉ፤ በደንም ውስጥ በሰላም ይተኛሉ። 26እነርሱንና በኰረብታዬ ዙሪያ ያሉትን ስፍራዎች እባርካለሁ።34፥26 ወይም እነርሱንና በኰረብታዬ ዙሪያ ያሉትን ስፍራዎች ለበረከት አደርጋቸዋለሁ በወቅቱም ዝናብ አወርድላቸዋለሁ፤ ዝናቡም የበረከት ዝናብ ይሆናል። 27የየሜዳው ዛፍ ፍሬ ይሰጣል፤ መሬቱም እህል ያበቅላል። ሕዝቡም በምድሪቱ ላይ በሰላም ይኖራሉ። የቀንበሮቻቸውን ማነቆ ሰብሬ በባርነት ከገዟቸው እጅ ሳድናቸው፣ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። 28ከእንግዲህ ለሌሎች ሕዝቦች ንጥቂያ አይዳረጉም፤ የዱር አራዊት አይቦጫጭቋቸውም፤ በሰላም ይኖራሉ፤ የሚያስፈራቸውም አይኖርም። 29ከእንግዲህ በምድሪቱ ላይ የራብ ተጠቂ እንዳይሆኑ፣ የአሕዛብንም ስድብ እንዳይሸከሙ ፍሬ በመስጠት የታወቀውን መሬት እሰጣቸዋለሁ። 30ከዚያም እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው ከእነርሱ ጋር እንደ ሆንሁ፤ የእስራኤል ቤት የሆኑት እነርሱም ሕዝቤ እንደ ሆኑ ያውቃሉ፣ ይላል ጌታ እግዚአብሔር31እናንተ በጎቼ የማሰማሪያዬ በጎች ያልኋችሁ፣ ሕዝብ ናችሁ፤ እኔም አምላካችሁ ነኝ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’ ”

New International Reader’s Version

Ezekiel 34:1-31

The Lord Will Be the Shepherd of His People

1A message from the Lord came to me. The Lord said, 2“Son of man, prophesy against the shepherds of Israel. Tell them, ‘The Lord and King says, “How terrible it will be for you shepherds of Israel! You only take care of yourselves. You should take good care of your flocks. 3Instead, you eat the butter. You dress yourselves with the wool. You kill the finest animals. But you do not take care of your flocks. 4You have not made the weak ones in the flock stronger. You have not healed the sick. You have not bandaged those who are hurt. You have not brought back those who have wandered away. You have not searched for the lost. When you ruled over them, you were mean to them. You treated them badly. 5So they were scattered because they did not have a shepherd. They became food for all of the wild animals. 6My sheep wandered all over the mountains and high hills. They were scattered over the whole earth. No one searched for them. No one looked for them.”

7“ ‘Shepherds, listen to the Lord’s message. He says, 8“My flock does not have a shepherd. Many of my sheep have been stolen. They have become food for all the wild animals. My shepherds did not care for my sheep. They did not even search for them. Instead, they only took care of themselves. And that is just as sure as I am alive,” announces the Lord and King. 9Shepherds, listen to the Lord’s message. 10The Lord and King says, “I am against the shepherds. I will hold them responsible for my flock. I will stop them from taking care of the flock. Then they will not be able to feed themselves anymore. I will save my flock from their mouths. My sheep will no longer be food for them.” ’ ”

11The Lord and King says, “I myself will search for my sheep. I will look after them. 12A shepherd looks after his scattered flock when he is with them. And I will look after my sheep. I will save them from all the places where they were scattered on a dark and cloudy day. 13I will bring them out from among the nations. I will gather them together from other countries. I will bring them into their own land. There they will eat grass on the mountains and in the valleys. And they will eat in all the fields of Israel. 14I will take care of them in the best grasslands. They will eat grass on the highest mountains of Israel. There they will lie down in the finest grasslands. They will eat grass in the best places on Israel’s mountains. 15I myself will take care of my sheep. I will let them lie down in safety,” announces the Lord and King. 16“I will search for the lost. I will bring back those who have wandered away. I will bandage the ones who are hurt. I will make the weak ones stronger. But I will destroy those who are fat and strong. I will take good care of my sheep. I will treat them fairly.”

17The Lord and King says, “You are my flock. I will judge between one sheep and another. I will judge between rams and goats. 18You already eat in the best grasslands. Must you also stomp all over the other fields? You already drink clear water. Must you also make the rest of the water muddy with your feet? 19Must my flock have to eat the grass you have stomped on? Must they drink the water you have made muddy?”

20So the Lord and King speaks to them. He says, “I myself will judge between the fat sheep and the skinny sheep. 21You push the other sheep around with your hips and shoulders. You use your horns to butt all the weak sheep. Finally, you drive them away. 22But I will save my sheep. They will not be carried off anymore. I will judge between one sheep and another. 23I will place one shepherd over them. He will belong to the family line of my servant David. He will take good care of them. He will look after them. He will be their shepherd. 24I am the Lord. I will be their God. And my servant from David’s family line will be the prince among them. I have spoken. I am the Lord.

25“I will make a covenant with them. It promises to give them peace. I will get rid of the wild animals in the land. Then my sheep can live safely in the desert. They can sleep in the forests. 26I will make them and the places surrounding my holy mountain of Zion a blessing. I will send down rain at the right time. There will be showers of blessing. 27The trees will bear their fruit. And the ground will produce its crops. The people will be secure in their land. I will break the chains that hold them. I will save them from the power of those who made them slaves. Then they will know that I am the Lord. 28The nations will not carry them off anymore. Wild animals will no longer eat them up. They will live in safety. And no one will make them afraid. 29I will give them a land that is famous for its crops. They will never again be hungry there. The nations will not make fun of them anymore. 30Then they will know that I am with them. I am the Lord their God. And the Israelites will know that they are my people,” announces the Lord and King. 31“You are my sheep. You belong to my flock. And I am your God,” announces the Lord and King.