ሕዝቅኤል 32 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 32:1-32

ስለ ፈርዖን የወጣ ሙሾ

1በዐሥራ ሁለተኛው ዓመት፣ በዐሥራ ሁለተኛው ወር፣ በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ለግብፅ ንጉሥ ለፈርዖን ሙሾ አውርድ፤ እንዲህም በለው፤

“ ‘አንተ በሕዝቦች መካከል እንደ አንበሳ፣

በባሕሮችም ውስጥ እንደ አስፈሪ አውሬ ነህ፤

በወንዞችህ የምትንቦጫረቅ፣

ውሃውን በእግርህ የምትመታ፣

ምንጮችን የምታደፈርስ ነህ።

3“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ብዙ ሕዝብ ይዤ፣

መረቤን በላይህ ላይ እጥላለሁ፤

በመረቤም ጐትተው ያወጡሃል።

4በምድር ላይ እጥልሃለሁ፤

ሜዳም ላይ እዘረጋሃለሁ፤

የሰማይ ወፎች ሁሉ እንዲሰፍሩብህ አደርጋለሁ፤

የምድር አራዊት ሁሉ በመስገብገብ ይበሉሃል።

5ሥጋህን በተራሮች ላይ እበታትነዋለሁ፤

የተረፈውንም በየሸለቆው እሞላዋለሁ።

6እስከ ተራሮች ባለው መንገድ ሁሉ፣

በሚፈስሰው ደምህ ምድሪቱን አርሳታለሁ፤

ሸለቆዎችም በሥጋህ ይሞላሉ።

7አንተን በማጠፋ ጊዜ ሰማያትን እሸፍናለሁ፤

ከዋክብታቸውንም አጨልማለሁ፤

ፀሓይን በደመና እሸፍናለሁ፤

ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም።

8በሰማይ የሚያበሩትን ብርሃናት ሁሉ፣

በአንተ ላይ አጨልማለሁ፤

በምድርህ ላይ ጨለማን አመጣለሁ፤

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

9በማታውቀው ምድር፣

በሕዝቦች መካከል ያንተን ጥፋት ሳመጣ፣32፥9 በዕብራይስጡም እንዲሁ ሲሆን ሰብዐ ሊቃናት ግን በአሕዛብ መካከል ወደ ምርኮ ሳመጣው ይላል

የብዙ ሕዝብን ልብ አስጨንቃለሁ።

10ሕዝቦች በአንተ ላይ ከደረሰው የተነሣ እንዲደነግጡ አደርጋለሁ፤

ሰይፌን በፊታቸው ስነቀንቅ፣

በአንተ ላይ ከደረሰው ሁኔታ የተነሣ ንጉሦቻቸው ይንቀጠቀጣሉ።

አንተ በምትወድቅበት ቀን፣

እያንዳንዳቸው ስለ ራሳቸው ሕይወት በመፍራት፣

በየቅጽበቱ ይርበደበዳሉ።

11“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤

“ ‘የባቢሎን ንጉሥ ሰይፍ፣

በአንተ ላይ ይመጣል።

12ከሕዝቦች ሁሉ እጅግ ጨካኝ በሆኑት፣

በኀያላን ሰዎች ሰይፍ፣

ያከማቸኸው ሰራዊት እንዲወድቅ አደርጋለሁ፤

የግብፅን ኵራት ያንኰታኵታሉ፤

የሰራዊቷም ብዛት ይጠፋል፤

13ብዙ ውሃ ባለበት አጠገብ ያለውን፣

የከብት መንጋዋን አጠፋለሁ፤

ከእንግዲህ የሰው እግር አይረጋግጠውም፤

የከብትም ኰቴ አያደፈርሰውም።

14ከዚያም ውሆቿን አጠራለሁ፤

ወንዞቿም እንደ ዘይት እንዲፈስሱ አደርጋለሁ፤

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

15ግብፅን ባድማ ሳደርጋት፣

ምድሪቱም ያላትን ሁሉ ያጣች ስትሆን፣

በዚያም የሚኖሩትን ሁሉ ስመታ፣

ያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’

16“ስለ እርሷ የሚያወርዱት ሙሾ ይህ ነው፤ የሕዝቦች ሴት ልጆች ያዜሙታል፤ ስለ ግብፅና ስለ ብዙ ሰራዊቷ ሁሉ ሙሾ ያወርዳሉ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።”

17በዐሥራ ሁለተኛው ዓመት፣ ከወሩም በዐሥራ አምስተኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 18“የሰው ልጅ ሆይ፤ ስለ ብዙው የግብፅ ሰራዊት አልቅስ፤ እርሷንና የኀያላንን ሕዝቦች ሴት ልጆች ወደ ጕድጓድ ከሚወርዱት ጋር ከምድር በታች አውርዳቸው። 19እንዲህም በላቸው፤ ‘እናንተ ከሌሎች የተለያችሁ ናችሁን? ውረዱ፤ ባልተገረዙትም መካከል ተጋደሙ።’ 20እነርሱም በሰይፍ በተገደሉት መካከል ይወድቃሉ፤ ሰይፉ ተመዝዟል፤ ከብዙ ሰራዊቷ ሁሉ ጋር ትጐተት። 21በመቃብርም32፥21 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል፤ በ27 ትም እንዲሁ ውስጥ ኀያላኑ መሪዎች ስለ ግብፅና ስለ ተባባሪዎቿ፣ ‘ወደ ታች ወርደዋል፤ በሰይፍ ከተገደሉትና ካልተገረዙትም ጋር በአንድ ላይ ተጋድመዋል’ ይላሉ።

22“አሦር ከመላው ሰራዊቷ ጋር በዚያ ትገኛለች፤ በሰይፍ በወደቁባትና በታረዱባት ሰዎች ሁሉ መቃብር ተከብባለች። 23መቃብራቸው በጥልቁ ጕድጓድ ውስጥ ነው፤ ሰራዊቷም በመቃብሯ ዙሪያ ተረፍርፏል። በሕያዋን ምድር ሽብርን የነዙ ሁሉ ታርደዋል፤ በሰይፍም ወድቀዋል።

24“ኤላም በዚያ አለች፤ ሰራዊቷም ሁሉ በመቃብሯ ዙሪያ አለ፤ ሁሉም ታርደዋል፤ በሰይፍ ወድቀዋል። በሕያዋን ምድር ሽብር የነዙ ሁሉ ሳይገረዙ ከምድር በታች ወርደዋል፤ ወደ ጕድጓድ ከወረዱት ጋር ዕፍረታቸውን ተሸክመዋል፤ 25በመቃብሯ ዙሪያ ካለው መላው ሰራዊቷ ጋር፣ በታረዱት መካከል መኝታ ተዘጋጅቶላታል። ሁሉም ያልተገረዙና በሰይፍ የተገደሉ ናቸው፤ ሽብራቸው በሕያዋን ምድር ስለ ተነዛ፣ ወደ ጕድጓድ ከሚወርዱት ጋር ዕፍረታቸውን ይሸከማሉ፤ በታረዱትም መካከል ይጋደማሉ።

26“ሞሳህና ቶቤል መቃብሮቻቸው በብዙ ሰራዊታቸው መቃብር ተከብበው ይገኛሉ፤ ሁሉም ያልተገረዙ ሲሆኑ፣ በሕያዋን ምድር ሽብራቸውን ስለ ነዙ በሰይፍ ተገድለዋል። 27ከዘመናት በፊት ከወደቁት ከኀያላን ሰዎች፣ ከእነዚያ ሰይፋቸውን ተንተርሰው፣ ጋሻቸውንም ደረታቸው ላይ ይዘው ከነሙሉ ትጥቃቸው ወደ መቃብር ከወረዱት ጋር አይጋደሙምን? የእነዚህ ተዋጊዎች ሽብር በሕያዋን ምድር ባሉት ኀያላን ላይ ቢደርስም፣ የኀጢአታቸው ቅጣት በዐጥንታቸው ላይ ይሆናል።

28“ፈርዖን ሆይ፤ አንተም እንደዚሁ ትሰበራለህ፤ በሰይፍ ከተገደሉት ከእነዚያ ካልተገረዙት ጋር ትጋደማለህ።

29“ኤዶምም በዚያ አለች፤ ንጉሦቿና ገዦቿም ሁሉ በዚያ አሉ፤ ኀይል የነበራቸው ቢሆኑም፣ በሰይፍ ከተገደሉት ጋር ተጋድመዋል፤ ወደ ጕድጓድ ከወረዱት ከእነዚያ ካልተገረዙትም ጋር ተኝተዋል።

30“የሰሜን ገዦች በሙሉ፣ ሲዶናውያንም ሁሉ በዚያ ይገኛሉ፤ ከዚህ በፊት በኀይላቸው ምክንያት ሽብር የፈጠሩ ቢሆኑም፣ ከታረዱት ጋር በኀፍረት ወረዱ፤ ሳይገረዙም በሰይፍ ከተገደሉት ጋር ይጋደማሉ፤ ወደ ጕድጓድ ከወረዱትም ጋር ኀፍረታቸውን ይሸከማሉ።

31“ፈርዖንና ሰራዊቱ ሁሉ ያዩአቸዋል፤ በሰይፍ ከተገደለበት ሰራዊትም ሁሉ ሐዘን ይጽናናል፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር32በሕያዋን ምድር ሽብር እንዲያስፋፋ ብፈቅድም እንኳ፣ ፈርዖንና ሰራዊቱ ሁሉ በሰይፍ ከተገደሉት ጋር ባልተገረዙት መካከል ይጋደማሉ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።”

Bibelen på hverdagsdansk

Ezekiels Bog 32:1-32

Dommen over Egyptens konge

1På den første dag i den 12. måned i det 12. år af vores eksil sagde Herren til mig: 2„Du menneske, syng en sørgesang for Egyptens konge:

Du var som en løve blandt nationerne,

som et uhyre fra havet fór du frem,

piskede Nilens vande op

og trampede bredderne til mudder.

3Men hør, hvad Herren siger til dig:

Jeg fanger dig i mit fiskenet,

sender min hær og trækker dig op,

4lader dig ligge på bredden og dø,

slænger dig ud i den øde ørken,

så himlens fugle slår ned på dig,

og jordens rovdyr mættes med dit kød.

5Jeg spreder dit kød ud over bjergene,

kaster dine knogler i dalenes kløfter.

6Jeg lader jorden drikke dit blod,

og bjergenes kløfter fyldes deraf.

7Når dommens dag rammer dig,

tildækker jeg himlens stjerner.

Solen bliver gemt bag sorte skyer,

og månens lys forsvinder.

8Jeg slukker alle himlens lys,

så hele dit land opsluges af mørke.

9Rygtet om din skæbne vil nå ud til lande,

som du aldrig har set eller hørt om,

og folkene dér vil fyldes af frygt.

10Mange folkeslag bliver lammet af rædsel,

og deres konger ryster af skræk,

når de ser, hvordan jeg svinger mit sværd

og lader det ramme dig med frygtelig kraft.

11For det er, hvad Gud Herren siger:

Babyloniens konges sværd skal ramme dig.

12Jeg sender verdens vældigste hær imod dig,

den er berømt for sin grusomhed.

Den raserer det, du er allermest stolt af,

og udrydder både folk og husdyr.

13Kvæget, der græsser langs floden, bliver udryddet.

Ingen hove skal længere mudre vandet til,

ingen menneskefødder forstyrre flodens ro.

14Nilens vand bliver klart og gennemsigtigt,

floden skal flyde som olivenolie, siger Herren.

15Når jeg lægger dit land øde

og udrydder din befolkning,

da vil folk indse, at jeg er Herren.

16Da skal denne klagesang synges.

Alle folkeslag skal stemme i

og sørge over Egyptens skæbne, siger Herren.”

17På den 15. dag i samme måned sagde Herren til mig: 18„Du menneske, sørg over Egypten, for jeg styrter landet ned i dødsriget sammen med andre, mægtige nationer.

19Du Egypten, er du mon bedre end de andre?

Kom ned og lig blandt de andre gudløse!

20Egypterne skal dø som alle andre.

Sværdet er draget og vil ramme dem alle.

21Dødsrigets helte tager imod dem med skadefryd,

giver dem plads iblandt alle de faldne.

‚Nu er de gudløse egyptere faldet,’ råber de.

‚Heltene er pludselig blevet så tavse.’

22Der ligger Assyriens mægtige fyrster.

Alle blev dræbt, de faldt for sværdet.

23De ligger i dødsrigets inderste kroge.

Skønt de spredte rædsel på jorden,

endte dog alle som offer for sværdet.

24Elams mægtige konger er der,

omgivet af deres faldne krigere.

Alle blev dræbt, de faldt for sværdet.

I live spredte de rædsel omkring sig.

Nu ligger de mellem de andre gudløse.

Deres skæbne blev som alle andres.

25Blandt dødsrigets dræbte fik de et hvilested,

omgivet af deres faldne krigere.

Alle de gudløse segnede for sværdet,

for de spredte rædsel i de levendes land.

Nu må de bide skammen i sig,

for de faldt selv for sværdet til sidst.

26Der ligger Mesheks og Tubals fyrster,

omgivet af deres faldne krigere.

I live spredte de rædsel omkring sig.

Nu ligger de mellem de andre gudløse.

27De ligger ikke blandt de gamle helte,

som fik en ærefuld begravelse

og fik deres våben med i dødsriget,

sværdet under hovedet og skjoldet over kroppen,

for de spredte rædsel i de levendes land.

28Egypten, dine krigere må ligge mellem de gudløse,

side om side med alle de andre dræbte.

29Der ligger Edoms konger og fyrster,

som fik deres grav blandt de slagne,

blandt de gudløse, der endte i døden.

30Alle nordens fyrster ligger slagne dernede,

side om side med folkene fra Sidon.

Alle de gudløse segnede for sværdet.

De spredte skræk og rædsel omkring sig,

men nu må de bide skammen i sig

sammen med de andre gudløse i graven.

31Når egypterkongen ender på det sted,

kan han se på de andre og trøste sig med,

at han ikke er den eneste, der tabte en krig.

32Egypterkongen og hele hans hær

spredte skræk og rædsel i de levendes land.

Nu ligger han blandt de gudløse og dræbte,

der faldt for sværdet, siger Gud Herren.”