ሕዝቅኤል 31 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 31:1-18

የሊባኖስ ዝግባ

1በዐሥራ አንደኛው ዓመት፣ በሦስተኛው ወር፣ በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ለግብፅ ንጉሥ ለፈርዖንና ስፍር ቍጥር ለሌለው ሕዝቡ እንዲህ በል፤

“ ‘በክብር ከአንተ ጋር ማን ሊወዳደር ይችላል?

3ለጫካው ጥላ የሆኑ የሚያማምሩ ቅርንጫፎች የነበሩትን፣

እጅግ መለሎ ሆኖ፣

ጫፉ ሰማይ የደረሰውን፣

የሊባኖስን ዝግባ አሦርን ተመልከት።

4ውሆች አበቀሉት፤

ጥልቅ ምንጮች አሳደጉት፤

ጅረቶቻቸው ፈሰሱ፤

የሥሮቹንም ዙሪያ ሁሉ አረሰረሱ፤

በመስኩ ላይ ወዳሉት ዛፎች ሁሉ፣

መስኖዎቻቸውን ለቀቁት።

5ስለዚህ በደን ካሉት ዛፎች ሁሉ፣

እጅግ ከፍ አለ፤

ቅርንጫፎቹ በዙ፤

ቀንበጦቹ ረዘሙ፤

ከውሃውም ብዛት የተነሣ ተስፋፉ።

6የሰማይ ወፎች ሁሉ፣

በቅርንጫፎቹ ላይ ጐጇቸውን ሠሩ፤

የምድር አራዊት ሁሉ፣

ከቅርንጫፎቹ ሥር ግልገሎቻቸውን ወለዱ።

ታላላቅ መንግሥታትም ሁሉ፣

ከጥላው ሥር ኖሩ።

7ከተንሰራፉት ቅርንጫፎቹ ጋር፣

ውበቱ ግሩም ነበር፤

ብዙ ውሃ ወዳለበት፣

ሥሮቹ ጠልቀው ነበርና።

8በእግዚአብሔር ገነት ያሉ ዝግባዎች፣

ሊወዳደሩት አልቻሉም፤

የጥድ ዛፎች፣

የእርሱን ቅርንጫፎች አይተካከሉትም፤

የአስታ ዛፎችም፣

ከእርሱ ቅርንጫፎች ጋር አይወዳደሩም፤

በእግዚአብሔር ገነት ያለ ማናቸውም ዛፍ፣

በውበት አይደርስበትም።

9በብዙ ቅርንጫፎች፣

ውብ አድርጌ ሠራሁት፤

በእግዚአብሔርም የአትክልት ቦታ፣

በገነት ያሉትን ዛፎች የሚያስቀና አደረግሁት።

10“ ‘ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ጥቅጥቅ ባለው ቅጠል ላይ ጫፉን ከፍ በማድረግ ራሱን በማንጠራራቱ፣ በርዝማኔውም በመኵራራቱ፣ 11እንደ ክፋቱ መጠን የሥራውን ይከፍለው ዘንድ፣ ለአሕዛብ ገዥ አሳልፌ ሰጠሁት። አውጥቼ ጥዬዋለሁ፤ 12ከአሕዛብ ወገን እጅግ ጨካኝ የሆኑትም ባዕዳን ሰዎች ቈራርጠው ጣሉት። ቀንበጦቹ በተራራዎቹና በሸለቆዎቹ ሁሉ ላይ ወድቀዋል፤ ቅርንጫፎቹም በውሃ መውረጃዎቹ ሁሉ ላይ ተሰባብረው ወድቀዋል፤ የምድሪቱ ሰዎች ሁሉ ከጥላው ሥር በመውጣት ትተውት ሄደዋል። 13የሰማይ ወፎች ሁሉ በወደቀው ዛፍ ላይ ሰፈሩ፤ የምድር አራዊት ሁሉ በወደቀው ዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ሰፈሩ። 14ስለዚህ በውሃ አጠገብ ያለ ማንኛውም ዛፍ፣ ጫፎቹን ችምችም ካለው ቅጠል በላይ ከፍ በማድረግ፣ ከእንግዲህ ራሱን በትዕቢት አያንጠራራም። ከእንግዲህ ውሃ በሚገባ ያገኘ ማንኛውም ዛፍ ወደዚህ ዐይነቱ ከፍታ አይደርስም። ሁሉም ከምድር በታች ወደ ጕድጓድ ከሚወርድ ሟች ጋር አብሮ እንዲሞት ተወስኖበታልና።”

15“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ወደ መቃብር31፥15 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል፤ እንዲሁም በ16 እና 17 በወረደበት ቀን ጥልቅ ምንጮችን ስለ እርሱ በሐዘን ሸፈንኋቸው፤ ወንዞቹን ገታሁ፤ ታላላቅ ፈሳሾችም ተቋረጡ። በእርሱም ምክንያት ሊባኖስን ጨለማ አለበስሁ፤ የደን ዛፎችም ሁሉ ደረቁ። 16ወደ ጕድጓድ ከሚሄዱት ጋር ወደ መቃብር ባወረድሁት ጊዜ ሲወድቅ በተሰማው ድምፅ አሕዛብ ደነገጡ። ከዚያም የዔድን ዛፎች ሁሉ፣ ምርጥና ልዩ የሆኑት የሊባኖስ ዛፎች፣ ውሃ የጠገቡትም ዛፎች ሁሉ ከምድር በታች ሆነው ተጽናኑ። 17ከአሕዛብ መካከል ከእርሱ ጋር ያበሩ፣ በጥላው ሥር የኖሩ፣ በሰይፍ ከሞቱት ጋር ለመቀላቀል ወደ መቃብር ወርደዋል።”

18“ ‘በዔድን ካሉት ዛፎች በውበትና በትልቅነት የሚወዳደርህ የትኛው ነው? ይሁን እንጂ አንተም እንደዚሁ ከዔድን ዛፎች ጋር ከመሬት በታች ትወርዳለህ፤ በሰይፍ ከተገደሉት፣ ካልተገረዙትም መካከል ትጋደማለህ።

“ ‘እንግዲህ ፈርዖንና ስፍር ቍጥር የሌለው ሕዝቡ የሚደርስባቸው ይህ ነው፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’ ”

Japanese Contemporary Bible

エゼキエル書 31:1-18

31

エジプトを象徴するレバノン杉

1エホヤキン王が捕囚となって十一年目の第三の月の一日、次のような主のことばがありました。

2-3「人の子よ、エジプトの王とその全国民に告げよ。

おまえはかつての大国アッシリヤと同じく、

まるでレバノン杉のようだ。

枝を大きく張って涼しい木陰を作り、

その先端は高く雲にまで達している。

4根は地下深く伸びて、枝はよく生い茂り、

水を回りの木々にも供給していた。

5どの木よりも高くそびえ立ち、

根から十分に水分を吸収して枝も大きく伸び、

こんもりと茂っていた。

6枝には鳥が巣を作り、木陰で家畜が子を産んだ。

このように世界の大国がみな、その木陰に住んだのだ。

7木はたくましく、美しかった。

深く根を張り、十分に水分を吸収していたからだ。

8神の園の中にも、

この木より高くそびえるものはなかった。

糸杉もこの木の枝とは比べようがなく、

その美しさにはかなわなかった。

9わたしが与えたその雄姿を、

エデンのすべての木がうらやましがった。」

10しかし、主はこう語ります。「エジプトは思い上がって、尊大になった。雲にまで達するほど自分を高くして、他を見下した。 11その罰として、わたしはエジプトを大国の手に渡して滅ぼす。わたしがエジプトを切り倒すのだ。 12国々から恐れられているバビロンからの軍隊を侵入させ、その木を切り倒して、地に投げ捨てさせる。枝はエジプトの山や谷や川に散らされる。その木陰に身を寄せていた者はみな、倒れたエジプトを見捨てて出て行く。 13いろいろの鳥が、倒れた木の小枝をむしり取り、野獣が枝の間に住みつくようになる。 14どんな国も、雲より高くそびえても、その繁栄を鼻にかけて思い上がってはならない。すべてのものは滅びるからだ。それらはみな、世界中のおごり高ぶる者とともに、地獄に落とされる。」

15主は語ります。「エジプトが滅んだ日に、わたしは大海原を喪に服させ、その潮の満ち干を止めてしまった。レバノンに喪服をまとわせ、その木々を嘆き悲しませた。 16エジプトがくずれ落ちる大音響で、多くの国を恐れさせた。エジプトと同罪の国々をも、いっしょに地獄に投げ込んだからだ。エデンでおごり高ぶっている他のすべての木々、レバノンのえり抜きの大木、根を深く下ろして水分を吸い上げた木々は、エジプトが共に地獄にいるのを見て慰められる。 17エジプトの同盟国も、いっしょに滅ぼされる。その木陰に宿っていた国々も、共に下界に下って行った。

18ああ、エジプトよ。おまえはエデンの木々、すなわち世界の国々の中で、その偉大さと栄光を誇っている。だが、他のすべての国々とともに地獄の穴に投げ込まれてしまう。おまえが見下していた国々のように、剣で切り殺されるのだ。」これがエジプト王とその大軍の運命だと、主は語ります。