ሕዝቅኤል 30 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 30:1-26

ስለ ግብፅ የወጣ ሙሾ

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ትንቢት ተናገር፤ እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ዋይ! በል፤ እንዲህም በል፤

“ወዮ ለዚያ ቀን!”

3ቀኑ ቅርብ ነው፤

የእግዚአብሔር ቀን ቅርብ ነው፤

የደመና ቀን፣

ለአሕዛብም የጥፋት ቀን ነው።

4በግብፅ ላይ ሰይፍ ይሆናል፤

በኢትዮጵያም ላይ ጭንቀት ይመጣል።

የታረዱት በግብፅ ሲወድቁ፣

ሀብቷ ይወሰዳል፤

መሠረቶቿም ይፈርሳሉ።

5ኢትዮጵያና ፉጥ፣ ልድያና መላው ዐረብ፣ ሊብያና30፥5 ዕብራይስጡ ኩብ ይላል። የቃል ኪዳኑ ምድር ሕዝብ ከግብፅ ጋር በአንድነት በሰይፍ ይወድቃሉ።

6“ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘የግብፅ ተባባሪዎች ይወድቃሉ።

የምትኵራራበት ብርታቷ ይወድቃል።

ከሚግዶል እስከ አስዋን፣

በውስጧ በሰይፍ ይወድቃሉ፤

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

7በባድማ መሬቶች መካከል፣

ባድማ ይሆናሉ፤

ከተሞቻቸውም፣

ከፈራረሱ ከተሞች መካከል ይሆናሉ።

8በግብፅ ላይ እሳት ስጭር፣

ረዳቶቿ ሁሉ ሲደቅቁ፣

በዚያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።

9“ ‘በዚያ ቀን ከእኔ ዘንድ መልእክተኞች በመርከብ ወጥተው ተዘልላ ከተቀመጠችበት ሁኔታ ለማውጣት ኢትዮጵያን ያስፈራሯታል፤ ግብፅ በጨለማ በምትዋጥበት ቀን ጭንቅ ይይዛቸዋል፤ ቀኑ በርግጥ ይመጣልና።

10“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘በባቢሎን ንጉሥ በናቡከደነፆር እጅ፣

ስፍር ቍጥር የሌለውን የግብፅን ሕዝብ እደመስሳለሁ።

11ከአሕዛብ ሁሉ እጅግ ጨካኝ የሆኑት፣ እርሱና ሰራዊቱ፣

ምድሪቱን ለማጥፋት እንዲመጡ ይደረጋል፤

ሰይፋቸውን በግብፅ ላይ ይመዝዛሉ፤

ምድሪቱንም ሬሳ በሬሳ ያደርጋሉ፤

12የአባይን ወንዝ ውሃ አደርቃለሁ፤

ምድሪቱን ለክፉ ሰዎች እሸጣለሁ፤

በባዕዳን እጅ፣ ምድሪቷንና በውስጧ

ያለውን ሁሉ ባድማ አደርጋለሁ፤

እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ።

13“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ጣዖታትን አጠፋለሁ፤

በሜምፊስ30፥13 ዕብራይስጡ ኖፍ ይለዋል፤ እንዲሁም በ16 ያሉትን ምስሎች እደመስሳለሁ።

ከእንግዲህ በግብፅ ገዥ አይኖርም፣

በምድሪቱም ላይ ፍርሀት እሰዳለሁ።

14ጳትሮስን ባድማ አደርጋለሁ፤

በጣኔዎስ ላይ እሳት እለኵሳለሁ፤

በቴብስ30፥14 ዕብራይስጡ ይለዋል፤ እንዲሁም በ15 እና 16 ላይ ቅጣት አመጣለሁ።

15የግብፅ ምሽግ በሆነችው፣

በሲን ላይ መዓቴን አፈስሳለሁ፤

ስፍር ቍጥር የሌለውን የቴብስን ሕዝብ አጠፋለሁ።

16በግብፅ ላይ እሳት አነድዳለሁ፤

ሲን በጭንቅ ትናጣለች፤

ቴብስ በማዕበል ትወሰዳለች፤

ሜምፊስ በማያቋርጥ ጭንቀት ውስጥ ትገባለች።

17የሄልዮቱና30፥17 ዕብራይስጡ አዌን (ወይም ኦን) ይለዋል የቡባስቱ30፥17 ዕብራይስጡ ፊ ቢሴት ይላል ጕልማሶች፣

በሰይፍ ይወድቃሉ፤

ከተሞቹ ራሳቸውም ይማረካሉ።

18የግብፅን ቀንበር በምሰብርበት ጊዜ፣

በጣፍናስ ቀኑ ይጨልማል፤

ከዚያም የተኵራራችበት ብርታት ይንኰታኰታል።

በደመና ትሸፈናለች፤

መንደሮቿም ይማረካሉ።

19ስለዚህ በግብፅ ላይ ቅጣቴን አመጣለሁ፤

እነርሱም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

20በዐሥራ አንደኛው ዓመት፣ በመጀመሪያው ወር በሰባተኛው ቀን፣ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 21“የሰው ልጅ ሆይ፤ የግብፅን ንጉሥ የፈርዖንን ክንድ ሰብሬአለሁ፤ ይፈወስ ዘንድ ክንዱ አልተጠገነም፤ ወይም ሰይፍ መያዝ ይችል ዘንድ እጁ በመቃ አልታሰረም። 22ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በግብፅ ንጉሥ በፈርዖን ላይ ተነሥቻለሁ፤ ደኅናውንና የተሰበረውን፣ ሁለቱንም ክንዶቹን እሰብራለሁ፤ ሰይፉም ከእጁ እንዲወድቅ አደርጋለሁ። 23ግብፃውያንን በሕዝቦች መካከል እበትናቸዋለሁ፤ በአገሮችም መካከል እዘራቸዋለሁ። 24የባቢሎንን ንጉሥ ክንድ አበረታለሁ፤ ሰይፌንም አስይዘዋለሁ፤ የፈርዖንን ክንድ ግን እሰብራለሁ፤ እርሱም በፊቱ ክፉኛ እንደ ቈሰለ ሰው ያቃስታል። 25የባቢሎንን ንጉሥ ክንድ አበረታለሁ፤ የፈርዖን ክንድ ግን ይዝላል፤ ሰይፌን በባቢሎን ንጉሥ እጅ ሳስይዝ፣ እርሱም ሲነቀንቀው፣ ያኔ እግዚአብሔር መሆኔን ያውቃሉ። 26በሕዝቦች መካከል እበትናቸዋለሁ፤ በአገሮችም መካከል እዘራቸዋለሁ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር መሆኔን ያውቃሉ።”

King James Version

Ezekiel 30:1-26

1The word of the LORD came again unto me, saying, 2Son of man, prophesy and say, Thus saith the Lord GOD; Howl ye, Woe worth the day! 3For the day is near, even the day of the LORD is near, a cloudy day; it shall be the time of the heathen. 4And the sword shall come upon Egypt, and great pain shall be in Ethiopia, when the slain shall fall in Egypt, and they shall take away her multitude, and her foundations shall be broken down.30.4 pain: or, fear 5Ethiopia, and Libya, and Lydia, and all the mingled people, and Chub, and the men of the land that is in league, shall fall with them by the sword.30.5 Libya: Heb. Phut30.5 men: Heb. children 6Thus saith the LORD; They also that uphold Egypt shall fall; and the pride of her power shall come down: from the tower of Syene shall they fall in it by the sword, saith the Lord GOD.30.6 from…: or, from Migdol to Syene 7And they shall be desolate in the midst of the countries that are desolate, and her cities shall be in the midst of the cities that are wasted. 8And they shall know that I am the LORD, when I have set a fire in Egypt, and when all her helpers shall be destroyed.30.8 destroyed: Heb. broken 9In that day shall messengers go forth from me in ships to make the careless Ethiopians afraid, and great pain shall come upon them, as in the day of Egypt: for, lo, it cometh. 10Thus saith the Lord GOD; I will also make the multitude of Egypt to cease by the hand of Nebuchadrezzar king of Babylon. 11He and his people with him, the terrible of the nations, shall be brought to destroy the land: and they shall draw their swords against Egypt, and fill the land with the slain. 12And I will make the rivers dry, and sell the land into the hand of the wicked: and I will make the land waste, and all that is therein, by the hand of strangers: I the LORD have spoken it.30.12 dry: Heb. drought30.12 all…: Heb. the fulness thereof 13Thus saith the Lord GOD; I will also destroy the idols, and I will cause their images to cease out of Noph; and there shall be no more a prince of the land of Egypt: and I will put a fear in the land of Egypt. 14And I will make Pathros desolate, and will set fire in Zoan, and will execute judgments in No.30.14 Zoan: or, Tanis 15And I will pour my fury upon Sin, the strength of Egypt; and I will cut off the multitude of No.30.15 Sin: or, Pelusium 16And I will set fire in Egypt: Sin shall have great pain, and No shall be rent asunder, and Noph shall have distresses daily. 17The young men of Aven and of Pi-beseth shall fall by the sword: and these cities shall go into captivity.30.17 Aven: or, Heliopolis30.17 Pi-beseth: or, Pubastum 18At Tehaphnehes also the day shall be darkened, when I shall break there the yokes of Egypt: and the pomp of her strength shall cease in her: as for her, a cloud shall cover her, and her daughters shall go into captivity.30.18 darkened: or, restrained 19Thus will I execute judgments in Egypt: and they shall know that I am the LORD.

20¶ And it came to pass in the eleventh year, in the first month, in the seventh day of the month, that the word of the LORD came unto me, saying, 21Son of man, I have broken the arm of Pharaoh king of Egypt; and, lo, it shall not be bound up to be healed, to put a roller to bind it, to make it strong to hold the sword. 22Therefore thus saith the Lord GOD; Behold, I am against Pharaoh king of Egypt, and will break his arms, the strong, and that which was broken; and I will cause the sword to fall out of his hand. 23And I will scatter the Egyptians among the nations, and will disperse them through the countries. 24And I will strengthen the arms of the king of Babylon, and put my sword in his hand: but I will break Pharaoh’s arms, and he shall groan before him with the groanings of a deadly wounded man. 25But I will strengthen the arms of the king of Babylon, and the arms of Pharaoh shall fall down; and they shall know that I am the LORD, when I shall put my sword into the hand of the king of Babylon, and he shall stretch it out upon the land of Egypt. 26And I will scatter the Egyptians among the nations, and disperse them among the countries; and they shall know that I am the LORD.