ሕዝቅኤል 28 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 28:1-26

በጢሮስ ንጉሥ ላይ የተነገረ ትንቢት

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ለጢሮስ ገዥ እንዲህ በለው፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ልብህ በትዕቢት ተወጥሮ፣

“እኔ አምላክ ነኝ፤

በአምላክ ዙፋን ላይ፣

በባሕሮችም ልብ ተቀምጫለሁ” አልህ።

ምንም እንኳ እንደ አምላክ ጠቢብ ነኝ ብለህ ብታስብም፣

አንተ ሰው እንጂ አምላክ አይደለህም።

3ከዳንኤል28፥3 ወይም ዳኔል፤ የዕብራይስጡን ቃል አጻጻፍ ስንመለከት ነቢዩ ዳንኤልን ሳይሆን ሌላን ሰው የሚያመለክት ነው። ይልቅ ጠቢብ ነህን?

ከአንተስ የተሰወረ ምስጢር የለምን?

4በጥበብህና በማስተዋልህ፣

የራስህን ሀብት አከማቸህ፤

ወርቅም ብርም፣

በግምጃ ቤትህ አጠራቀምህ።

5በንግድ ሥራ እጅግ ከመራቀቅህ የተነሣ፣

በሀብት ላይ ሀብት አካበትህ፤

ከሀብትህ ብዛት የተነሣም፤

ልብህ በትዕቢት ተወጠረ።

6“ ‘ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘እንደ አምላክ ጥበበኛ ነኝ፤ ብለህ

ስለምታስብ፣

7ከአሕዛብ መካከል እጅግ ጨካኞች የሆኑትን ባዕዳን፣

በአንተ ላይ አመጣለሁ፤

በጥበብህ ውበት ላይ ሰይፋቸውን ይመዝዛሉ፤

ታላቅ ክብርህንም ያረክሳሉ።

8ወደ ጕድጓድ ያወርዱሃል፤

በጥልቁም ባሕር ውስጥ፣

በባሕሮችም ልብ ውስጥ አስከፊ ሞት ትሞታለህ።

9ታዲያ በገዳዮችህ ፊት፣

“አምላክ ነኝ” ትላለህን?

በገዳዮችህ እጅ ስትገባ፣

አንተ ሰው እንጂ አምላክ አይደለህም።

10በባዕዳን እጅ፣

ያልተገረዙትን ሰዎች አሟሟት ትሞታለህ፤

እኔ ተናግሬአለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’ ”

11የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 12“የሰው ልጅ ሆይ፤ ስለ ጢሮስ ንጉሥ ሙሾ አውርድ፤ እንዲህም በለው፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ጥበብን የተሞላህ፣ ፍጹም ውበትን የተላበስህ፣

የፍጹምነት ምሳሌ ነበርህ።

13በእግዚአብሔር የአትክልት ቦታ፣

በዔድን28፥13 ወይም ላፒስ ላዙሊ ነበርህ፤

እያንዳንዱ የከበረ ድንጋይ አስጊጦህ ነበር፤

ሰርድዮን፣ ቶጳዝዮን፣ አልማዝ፣

መረግድ፣ ኢያሰጲድ፣ ሰንፔር፣

በሉር፣ ቢረሌና የከበረ ዕንቍ።28፥13 ከእነዚህ የከበሩ ድንጋዮች መካከል አንዳንዶቹ ትክክለኛ ማንነታቸው ተለይቶ አይታወቅም

ልብስህም የሚያብረቀርቅ ዕንወርቅ ነበር፤

የተዘጋጁትም አንተ በተፈጠርህበት ዕለት ነበር።

14ጠባቂ ኪሩብ ሆነህ ተቀብተህ ነበር፤

ለዚሁም ሾምሁህ፤

በእግዚአብሔር ቅዱስ ተራራ ላይ ነበርህ፤

በእሳት ድንጋዮች መካከል ተመላለስህ።

15ከተፈጠርህበት ቀን ጀምሮ፣

ክፋት እስከ ተገኘብህ ድረስ፣

በመንገድህ ነቀፌታ አልነበረብህም።

16ንግድህ ስለ ደረጀ፣

በዐመፅ ተሞላህ፣

ኀጢአትም ሠራህ፤

ስለዚህ ከእግዚአብሔር ተራራ በውርደት አሳደድሁህ፤

ጠባቂ ኪሩብ ሆይ፤ ከእሳት ድንጋዮች

መካከል አስወጣሁህ።

17በውበትህ ምክንያት፣

ልብህ ታበየ፤

ከክብርህ ታላቅነት የተነሣም፣

ጥበብህን አረከስህ።

ስለዚህ ወደ ምድር ወረወርሁህ፤

ለነገሥታት ትዕይንት አደረግሁህ።

18በኀጢአትህና በተጭበረበረው ንግድህ ብዛት፣

መቅደስህን አረከስህ።

ስለዚህ እሳት ከአንተ እንዲወጣ አደረግሁ፤

እርሱም በላህ፤

በሚመለከቱህ ሁሉ ፊት፣

በምድር ላይ ዐመድ አደረግሁህ።

19የሚያውቁህን አሕዛብ ሁሉ፣

ሁኔታህ አስደንግጧቸዋል፤

መጨረሻህ የሚያሳዝን ሆነ፤

ከእንግዲህ ህልውና የለህም።’ ”

በሲዶን ላይ የተነገረ ትንቢት

20የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 21“የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን ወደ ሲዶና አዙር፤ ትንቢትም ተናገርባት፤ 22እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ሲዶን ሆይ፤ በአንቺ ላይ ተነሥቻለሁ፤

በውስጥሽ እከብራለሁ፤

ቅጣትን ሳመጣባት፣

ቅድስናዬንም በውስጧ ስገልጥ፣

እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።

23በእርሷ ላይ መቅሠፍት አመጣለሁ፤

በመንገዶቿ ላይ ደም እንዲፈስስ አደርጋለሁ፤

ከየአቅጣጫው በሚመጣ ሰይፍ፣

የታረዱት በውስጧ ይወድቃሉ፤

ከዚያም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።

24“ ‘ከእንግዲህ ወዲያ የእስራኤል ሕዝብ የሚያሠቃይ አሜከላና የሚወጋ እሾኽ የሆኑ ጎረቤቶች አይኖሯቸውም፤ ከዚያም እኔ ጌታ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።

25“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የእስራኤልን ሕዝብ ከተበተኑባቸው አገሮች መካከል በምሰበስብበት ጊዜ፣ አሕዛብ እያዩ ቅድስናዬን በመካከላቸው እገልጣለሁ፤ ከዚያም በገዛ ምድራቸው ይኖራሉ፤ ይህም ለባሪያዬ ለያዕቆብ የሰጠሁት ነው። 26በዚያም በሰላም ይኖራሉ፤ ቤቶች ይሠራሉ፤ የወይን ተክል ቦታም ያበጃሉ። ያጣጣሏቸው ጎረቤቶቻቸውን ሁሉ በምቀጣበት ጊዜ እነርሱ በሰላም ይኖራሉ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

Bibelen på hverdagsdansk

Ezekiels Bog 28:1-26

Profeti imod fyrsten over Tyrus

1Herren sagde til mig: 2„Du menneske, sig til fyrsten over Tyrus:

Du er så stolt og hovmodig,

at du tror, du selv er en gud.

Du sidder på din høje trone,

hersker over havet og praler.

Men du er kun et menneske,

der bilder sig ind at være en gud.

3Du tror, du er klogere end Daniel

og kender alle hemmeligheder.

4Du brugte din visdom og forstand

til at samle mængder af guld og sølv.

5Dit handelstalent gjorde dig rig,

men din rigdom gjorde dig hovmodig.

6Derfor siger Gud Herren:

Fordi du tror, at du selv er en gud,

7sender jeg en grusom fjendehær,

der gør ende på din rigdom og pragt.

8Til dødsriget sender de dig ned,

du bliver dræbt og kastet i havet.

9Vil du mon fortsat hævde, du er en gud,

når fjenderne er ved at slå dig ihjel?

I hænderne på dem er du ingen gud,

men kun et almindeligt menneske.

10Du skal dø som en hund for de fremmedes hånd.

Jeg, Herren har talt.”

11Endvidere sagde Herren til mig: 12„Du menneske, istem en klagesang over Tyrus’ fyrste og sig til ham:

Engang var du fuldkommen,

smuk og fuld af visdom.

13Du levede som i Paradis,

smykket med utallige juveler:

rubin, topas og diamant,

krysolit, onyks og jaspis,

safir, granat og smaragd.

Alle juveler var indsat i guld,

de lå klar til dig ved din fødsel.

14Jeg satte dig som en kerub,

der skulle vogte og beskytte

det hellige bjerg, jeg havde skabt,

Du vandrede blandt funklende ædelsten.

15Der var intet at udsætte på dig

fra den dag, du blev født,

indtil din ondskab blev afsløret.

16Din store rigdom gjorde dig korrupt,

så vold og synd fyldte dit hjerte.

Da jog jeg dig bort fra mit hellige bjerg

og de funklende ædelsten, du skulle beskytte.

Jeg slog dig ned, du vældige kerub.

17Din skønhed gjorde dig stolt,

din rigdom spændte ben for din visdom.

Derfor kastede jeg dig til jorden

som en advarsel for andre fyrster.

18Din uhæderlige handel

afsporede din gudsdyrkelse.

Derfor lod jeg ild bryde frem og fortære dig,

så du blev til aske på jorden for alles øjne.

19Alle var skrækslagne over din skæbne.

Du blev et skræmmende eksempel

ved din totale og endelige udslettelse.”

Profeti imod Sidon

20Herren sagde til mig:

21„Du menneske, vend dig mod Sidon og profetér over byen. 22Sig til den:

Sidon, jeg er din fjende,

og jeg vil demonstrere min magt på dig.

Alle skal få at se, at jeg er Herren,

når jeg åbenbarer min hellighed på dig

ved at straffe dig for dine synder.

23Jeg sender epidemier og krig,

så blodet flyder i gaderne.

Fjenden angriber fra alle sider

og slår folk ned til højre og venstre.

Da vil du indse, at jeg er Herren.

Et løfte til Guds folk

24Israels nabofolk skal ikke længere stikke mit folk som tidsler og torne. Alle I, som nu håner mit folk, skal få at se, at jeg er Herren.

25Hør, hvad Herren siger: Når jeg samler Israels folk fra de folkeslag, de er spredt iblandt, og fører dem tilbage til deres eget land, det land, jeg gav min tjener Jakob, da vil alle folk indse, at jeg er en hellig og mægtig Gud. 26Derefter skal mit folk bo trygt i deres land, bygge huse og plante vingårde, mens jeg straffer alle dem, som behandlede dem med foragt. Da vil de indse, at jeg er Herren, deres Gud.”