ሕዝቅኤል 26 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 26:1-21

በጢሮስ ላይ የተነገረ ትንቢት

1በዐሥራ አንደኛው ዓመት፣ በመጀመሪያው ቀን፣ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ! ጢሮስ ስለ ኢየሩሳሌም፣ ‘ዕሠይ! የሕዝቦች በር ተሰበረች፤ ደጆቿም ወለል ብለው ተከፈቱልኝ፤ እንግዲህ እርሷ ስለ ፈራረሰች እኔ እከብራለሁ’ ብላለችና፤ 3ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ጢሮስ ሆይ፤ እነሆ በአንቺ ላይ ተነሥቻለሁ፤ ባሕር ሞገዷን እንደምታስነሣ፣ ብዙ ሕዝብ አስነሣብሻለሁ። 4የጢሮስን ቅጥሮች ያወድማሉ፤ ምሽጎቿንም ያፈርሳሉ። ዐፈሯን ከላይዋ ጠርጌ የተራቈተ ዐለት አደርጋታለሁ። 5እኔ ልዑል እግዚአብሔር ተናግሬአለሁና፤ በባሕር ውስጥ የመረብ ማስጫ ቦታ ትሆናለች፤ አሕዛብም ይበዘብዟታል፤ 6መኻል አገር ያሉ ሰፈሮቿም በሰይፍ ይወድማሉ፤ በዚያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’

7“ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ ‘የነገሥታት ንጉሥ የሆነውን የባቢሎንን ንጉሥ ናቡከደነፆርን26፥7 በዕብራይስጥ ናቡከደነፆር የሚለው ቃል አማራጭ ትርጕም ናቡካድረፃር ነው፤ በዚህ ክፍልና በአብዛኛው በሕዝቅኤልና በኤርምያስ መጽሐፍ ውስጥ እንደዚሁ ነው። ከፈረሶችና ከሠረገሎች ጋር፣ ከፈረሰኞችና ከታላቅ ሰራዊትም ጋር ከሰሜን በጢሮስ ላይ አመጣለሁ። 8እርሱ መኻል አገር ያሉ ሰፈሮችሽን በሰይፍ ያወድማቸዋል፤ በዙሪያሽ ካብ ይክባል፤ እስከ ቅጥሮችሽ ጫፍ ድረስ ዐፈር ይደለድልብሻል፤ ጋሻውንም በአንቺ ላይ ያነሣል። 9ግንብ መደርመሻውን በቅጥሮቿ ላይ ያነጣጥራል፤ በመሣሪያም ምሽጎችሽን ያፈርሳል። 10ከፈረሶቹ ብዛት የተነሣ ዐቧራ ይሸፍንሻል፤ ሰዎች ቅጥሮቿ ወደ ፈረሱ ከተማ እንደሚገቡ እርሱ በበሮችሽ በሚገባበት ጊዜ፣ ከፈረሶቹና ከጋሪዎቹ፣ ከሠረገሎቹም ድምፅ የተነሣ ቅጥሮችሽ ይናወጣሉ። 11መንገዶችሽ ሁሉ በፈረሶቹ ኰቴ ይረጋገጣሉ፤ ሕዝብሽን በሰይፍ ይገድላል፤ ታላላቅ ምሰሶዎችሽ ወደ ምድር ይወድቃሉ። 12ሀብትሽን ይዘርፋሉ፤ ሸቀጥሽን ይበዘብዛሉ፤ ቅጥሮችሽን ያፈርሳሉ፤ የተዋቡ ቤቶችሽን ያወድማሉ፤ ድንጋይሽን፣ ዕንጨትሽንና የግንቦች ፍርስራሽ ወደ ባሕር ይጥላሉ። 13ዘፈንሽን ጸጥ አደርጋለሁ፤ ከእንግዲህም የበገናሽ ድምፅ አይሰማም። 14የተራቈተ ዐለት አደርግሻለሁ፤ የመረብ ማስጫ ቦታ ትሆኛለሽ፤ እንደ ገናም ተመልሰሽ አትሠሪም፤ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁና፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’

15“ጌታ እግዚአብሔር ጢሮስን እንዲህ ይላል፤ ‘የቈሰሉት ሲያቃስቱ፣ በውስጥሽም ጭፍጨፋ ሲካሄድ፣ ከውድቀትሽ ድምፅ የተነሣ ደሴቶች አይነዋወጡምን? 16የባሕር ጠረፍ መሳፍንት ሁሉ ከዙፋኖቻቸው ይወርዳሉ፤ መጐናጸፊያቸውን ይጥላሉ፤ ወርቀ ዘቦ ልብሳቸውን ያወልቃሉ። ፍርሀት ተከናንበው በመሬት ላይ በመቀመጥ ባለ ማቋረጥ፣ እየተንቀጠቀጡ በአንቺ ላይ በደረሰው ነገር ይሸበራሉ፤’ 17ስለ አንቺም እንዲህ ብለው ሙሾ ያወርዳሉ፤

“ ‘በባሕር ሰዎች የሚኖሩብሽ፣

ባለ ዝናዋ ከተማ ሆይ፤ እንዴት ጠፋሽ!

ከነዋሪዎችሽ ጋር፣

የባሕር ላይ ኀያል ነበርሽ፤

በዚያ በሚኖሩትም ሁሉ ዘንድ

የተፈራሽ ነበርሽ።

18አሁን በመውደቂያሽ ቀን፣

በጠረፍ ያሉ አገሮች ተናወጡ፤

ከመፍረስሽም የተነሣ፤

በባሕር ውስጥ ያሉ ደሴቶች ተደናገጡ።’

19“ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ሰው እንደማይኖርባቸው ከተሞች ባድማ ሳደርግሽ፣ የውቅያኖስንም ውሃ በላይሽ አድርጌ በቀላይ ስሸፍንሽ፣ 20የጥንት ዘመን ሰዎች ወደ ገቡበት ጕድጓድ ከሚወርዱት ጋር አወርድሻለሁ፤ ወደ ጕድጓድ ከሚወርዱት ጋር በጥንቱ ፍርስራሽ ከምድር በታች አኖርሻለሁ፤ ከዚህም በኋላ በሕያዋን ምድር ተመልሰሽ ቦታ አታገኚም፤26፥20 ከሰብዐ ሊቃናት ጋር ተመሳሳይ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን ተመለሱ፤ ክብርን እሰጣለሁ ይላል። 21መጨረሻሽን አሳዛኝ አደርጋለሁ፤ ከእንግዲህም አትኖሪም፤ ትፈለጊያለሽ፤ ከቶም አትገኚም፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’ ”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以西结书 26:1-21

预言泰尔遭审判

1第十一年十一月一日,耶和华对我说: 2“人子啊,泰尔讥笑耶路撒冷说,‘哈哈!那通往列国的门户已遭破坏,城门向我大开,她已荒凉,我必兴盛。’ 3所以主耶和华说,‘泰尔啊,我要跟你作对,我要激起多国来攻击你,就像大海掀起波浪一样。 4他们要破坏你的墙垣,拆毁你的城楼。我要铲净你的瓦砾,使你成为光秃秃的磐石, 5在海中做晒网的地方,你必被列国掳掠,因为我已宣告。这是主耶和华说的。 6你陆地上的居民必死于刀下,这样你就知道我是耶和华。’

7“主耶和华说,‘我要使那王中之王的巴比伦尼布甲尼撒率领大队人马、战车和骑兵从北方来攻打泰尔8他必用刀剑杀戮你陆地上的居民,建垒筑台围困你,举着盾牌攻击你。 9他必用撞城锤击破你的城墙,用铁锤捣毁你的城楼。 10他人马众多,扬起的尘土足以遮盖你。他要攻破你的城池,进入你的城门,他的骑兵、军需车和战车要震动你的城墙。 11他战马的铁蹄必踏遍你的街道。他必挥刀屠杀你的居民,推倒你坚固的神柱, 12掠夺你的财物,摧毁你的城墙,夷平你华丽的房屋,把你的石头、木头和瓦砾抛到海里。 13我必使你的歌声消逝,琴音断绝。 14我要使你成为光秃秃的磐石,做晒网的地方,你必不得重建,因为我耶和华已经宣告。这是主耶和华说的。’

15“主耶和华对泰尔这样说,‘你倾覆的时候,你中间的杀戮声和受伤之人的惨叫声岂不震动沿海地区吗? 16沿海诸王因你而恐惧,都从宝座上下来,除去王袍,脱掉锦衣,坐在地上发抖。 17他们必为你唱哀歌说,

“‘你这海上众民居住的名城,

向来称雄海上,威震邻邦,

现在怎么被毁灭了呢?

18你倾覆的日子,

沿海各国都战战兢兢,

众海岛看见你被毁灭,

都心惊胆战。’

19“主耶和华说,‘我要使你成为荒无人烟的城邑,我要使海水上升淹没你。 20那时,我要使你与那些堕入阴间的人一同下到作古之人那里,使你与那些堕入阴间的人一同住在大地深处久已荒凉的地方,好让你荒无人烟,在活人之地毫无尊荣。 21我使你遭受可怕的灾难,你便不复存在,就是有人寻找你,也永远找不到,这是主耶和华说的。’”