ሕዝቅኤል 25 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 25:1-17

በአሞን ላይ የተነገረ ትንቢት

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን ወደ አሞናውያን አድርገህ፣ ትንቢት ተናገርባቸው፤ 3እንዲህም በላቸው፤ ‘የጌታ፣ እግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ መቅደሴ በረከሰ ጊዜ፣ የእስራኤልም ምድር ባድማ በሆነች ጊዜ፣ የይሁዳም ቤት ተማርኮ በተወሰደ ጊዜ፣ “ዕሠይ” ብላችኋልና፣ 4ለምሥራቅ ሕዝብ ትገዙ ዘንድ አሳልፌ እሰጣችኋለሁ፤ እነርሱም በመካከላችሁ ይሰፍራሉ፤ ድንኳኖቻቸውንም በዚያ ይተክላሉ፤ ፍሬያችሁን ይበላሉ፤ ወተታችሁንም ይጠጣሉ። 5የራባን ከተማ የግመሎች መሰማሪያ፣ አሞንንም የበጎች መመሰጊያ አደርጋለሁ፤ በዚያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። 6ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ በልባችሁ ክፋት ሁሉ፣ በእስራኤል ውድቀት ላይ በመደሰት በእጃችሁ አጨብጭባችኋልና፤ በመዝለልም ጨፍራችኋልና 7ክንዴን በእናንተ ላይ አነሣለሁ፤ በአሕዛብ እንድትበዘበዙ አደርጋለሁ፤ ከሕዝቦች መካከል አውጥቼ፣ ከአገሮችም ለይቼ አጠፋችኋለሁ፤ እደመስሳችኋለሁም። በዚያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።’ ”

በሞዓብ ላይ የተነገረ ትንቢት

8“ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ሞዓብና ሴይር፣ “እነሆ የይሁዳ ቤት እንደ ሌሎቹ አሕዛብ ሁሉ ሆነ” ብለዋልና፤ 9በምድሪቱ ድንበር ላይ ካሉትና ክብሯ ከሆኑት ከተሞች ከቤት የሺሞት፣ ከበአልሜዎንና ከቂርያታይም ጀምሬ የሞዓብን ዐምባ እገልጣለሁ። 10ሞዓባውያንንም ከአሞናውያን ጋር ይገዙላቸው ዘንድ፣ ለምሥራቅ ሕዝብ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ፤ አሞናውያን በአሕዛብ ዘንድ ከእንግዲህ መታሰቢያ አይኖራቸውም። 11ሞዓብንም እቀጣለሁ፤ በዚያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

በኤዶም ላይ የተነገረ ትንቢት

12“ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ኤዶም የይሁዳን ቤት ተበቅሏልና፤ በዚህም በደለኛ ሆኗልና፤ 13ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ክንዴን በኤዶም ላይ አነሣለሁ፤ ሰዎቹንና እንስሶቻቸውን እገድላለሁ፤ ባድማ አደርጋታለሁ፤ ከቴማንም ጀምሮ እስከ ድዳን ድረስ በሰይፍ ይወድቃሉ። 14በሕዝቤ በእስራኤል አማካይነት ኤዶምን እበቀላለሁ፤ እነርሱም እንደ ቍጣዬና እንደ መዓቴ መጠን በኤዶም ሕዝብ ላይ ያደርጋሉ፤ ኤዶማውያንም በቀሌን ያውቃሉ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’ ”

በፍልስጥኤም ላይ የተነገረ ትንቢት

15“ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ፍልስጥኤማውያን በቂም ተነሣሥተው በክፉ ልብ ተበቅለዋልና፣ ይሁዳንም በቈየ ጠላትነት ለማጥፋት ፈልገዋልና፤ 16ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ክንዴን በፍልስጥኤማውያን ላይ አነሣለሁ፤ ከሊታውያንንም እቈርጣለሁ፤ በባሕሩ ጠረፍ ላይ የቀሩትንም አጠፋለሁ። 17በታላቅ በቀል እበቀላቸዋለሁ፤ በመዓቴም እቀጣቸዋለሁ፤” በምበቀላቸውም ጊዜ፣ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

Thai New Contemporary Bible

เอเสเคียล 25:1-17

คำพยากรณ์กล่าวโทษอัมโมน

1พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าว่า 2“บุตรมนุษย์เอ๋ย จงประจันหน้ากับชาวอัมโมน และพยากรณ์กล่าวโทษพวกเขา 3จงกล่าวกับพวกเขาว่า ‘จงฟังพระดำรัสของพระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิต พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า เนื่องจากเจ้าสมน้ำหน้าสถานนมัสการของเราที่ถูกย่ำยี และสมน้ำหน้าดินแดนอิสราเอลที่ถูกทำให้เริศร้าง และสมน้ำหน้าชาวยูดาห์เมื่อเขาตกเป็นเชลย 4ฉะนั้นเราจะมอบเจ้าให้เป็นกรรมสิทธิ์ของชาวตะวันออก พวกเขาจะตั้งค่ายและตั้งเต็นท์ในหมู่พวกเจ้า พวกเขาจะกินพืชผลและดื่มนมของเจ้า 5เราจะทำให้รับบาห์กลายเป็นทุ่งหญ้าสำหรับอูฐ และอัมโมนเป็นที่พักสำหรับฝูงแกะ แล้วเจ้าจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์ 6เพราะพระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า เนื่องจากเจ้าปรบมือกระทืบเท้า และกระหยิ่มยิ้มย่องด้วยใจคิดร้ายต่อดินแดนอิสราเอล 7ฉะนั้นเราจะลงมือทำโทษเจ้า และมอบเจ้าให้ชนชาติต่างๆ ปล้นชิง เราจะทำให้เจ้าสิ้นชาติและไม่มีประเทศของเจ้าอีก เราจะทำลายล้างเจ้า แล้วเจ้าจะได้รู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์’ ”

คำพยากรณ์กล่าวโทษโมอับ

8“พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสว่า ‘เนื่องจากโมอับและเสอีร์กล่าวว่า “ดูเถิด พงศ์พันธุ์ยูดาห์ก็กลายเป็นเหมือนชนชาติอื่นๆ ทั้งปวง” 9ฉะนั้น เราจะเปิดฐานกำลังของโมอับ เริ่มตั้งแต่เมืองชายแดนต่างๆ ได้แก่ เบธเยชิโมท บาอัลเมโอน และคีริยาธาอิม ซึ่งเป็นศักดิ์ศรีของดินแดนนั้น 10เราจะมอบโมอับพร้อมทั้งชาวอัมโมนให้เป็นกรรมสิทธิ์ของชาวตะวันออก เพื่อชนชาติทั้งหลายจะไม่นึกถึงอัมโมนอีก 11และเราจะลงโทษโมอับ พวกเขาจะได้รู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์’ ”

คำพยากรณ์กล่าวโทษเอโดม

12“พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสว่า ‘เนื่องจากเอโดมแก้แค้นพงศ์พันธุ์ยูดาห์อย่างโหดเหี้ยม และผิดมากที่ทำเช่นนั้น 13ฉะนั้นพระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า เราจะลงมือทำโทษเอโดม ประหารทั้งผู้คนและสัตว์ เราจะทิ้งมันให้เริศร้าง และคนทั้งหลายจากเทมานถึงเดดานจะล้มตายด้วยคมดาบ 14เราจะแก้แค้นเอโดมโดยอาศัยน้ำมืออิสราเอลประชากรของเรา และพวกเขาจะจัดการกับเอโดมตามโทสะและความเกรี้ยวกราดของเรา เพื่อพวกเขาจะรู้จักการแก้แค้นของเรา พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศดังนั้น’ ”

คำพยากรณ์กล่าวโทษฟีลิสเตีย

15“พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสว่า ‘เนื่องจากชาวฟีลิสเตียอาฆาตและแก้แค้นด้วยใจชั่วร้าย และมุ่งทำลายยูดาห์เพราะเป็นศัตรูกันมาตั้งแต่โบราณ 16ฉะนั้นพระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า เรากำลังจะลงมือทำโทษฟีลิสเตีย และกำจัดชาวเคเรธี และทำลายล้างคนทั้งหลายที่เหลืออยู่ตามชายฝั่ง 17เราจะแก้แค้นพวกเขาครั้งใหญ่ และลงโทษพวกเขาด้วยความเกรี้ยวกราด แล้วพวกเขาจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์เมื่อเราแก้แค้นพวกเขา’ ”