ሕዝቅኤል 22 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 22:1-31

የኢየሩሳሌም ኀጢአት

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤

2“የሰው ልጅ ሆይ፤ አትፈርድባትምን? ደም በምታፈስሰው በዚህች ከተማ ላይ አትፈርድባትምን? ጸያፍ ተግባሯን ፊት ለፊት ንገራት፤ 3እንዲህም በላት፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በመካከልሽ ደምን በማፍሰስና ጣዖታትን በመሥራት ራስሽን የምታረክሺ፣ ፍርድንም በራስሽ ላይ የምታፈጥኚ ከተማ ሆይ፤ 4ባፈሰስሽው ደም በድለሻል፤ በሠራሽውም ጣዖት ረክሰሻል፤ ከዚህም የተነሣ ቀንሽን አቅርበሻል፤ ዕድሜሽንም አሳጥረሻል። ስለዚህ ለአሕዛብ መዘባበቻ፣ ለአገሩም ሁሉ መሣለቂያ አደርግሻለሁ። 5አንቺ የተዋረድሽና ሽብር የሞላብሽ ሆይ፤ በቅርብም በሩቅም ያሉ ይሣለቁብሻል።

6“ ‘እነሆ በመካከልሽ ያለ እያንዳንዱ የእስራኤል መስፍን ደም ለማፍሰስ ሥልጣኑን ይጠቀማል። 7አባቶችና እናቶች በውስጥሽ ተዋረዱ፤ መጻተኞች ተጨቈኑ፤ ድኻ አደጎችና መበለቶች ተንገላቱ። 8ንዋያተ ቅድሳቴን አቃለልሽ፤ ሰንበታቴንም አረከስሽ። 9ደምን ለማፍሰስ ወሬ የሚያቀብሉ በውስጥሽ አሉ፤ በኰረብታ ቤተ ጣዖት የተሠዋውን የሚበሉና ዝሙትን የሚፈጽሙ ሰዎች በመካከልሽ ይገኛሉ። 10የአባታቸውን መኝታ የሚደፍሩ ሰዎች በውስጥሽ አሉ፤ በሥርዐቱ መሠረት ንጹሕ ባልሆኑበት በወር አበባቸው ጊዜ ሴቶችን በማስገደድ የሚደፍሩ በመካከልሽ ይገኛሉ። 11በውስጥሽ አንዱ የባልንጀራውን ሚስት ያባልጋል፤ ሌላውም የልጁን ሚስት ያስነውራል፤ ሌላው ደግሞ የገዛ እኅቱ የሆነችውን የአባቱን ልጅ ይደፍራል። 12በመካከልሽ ያሉ ሰዎች ደም ለማፍሰስ ጕቦ ይቀበላሉ፤ አንቺም ዐራጣና ከፍተኛ ወለድ22፥12 ወይም ዐራጣና ወለድ በመውሰድ ከባልንጀራሽ የማይገባ ትርፍ ዘረፍሽ፤ እኔንም ረስተሻል፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር

13“ ‘ያለ አግባብ ባገኘሽው ጥቅምና በመካከልሽ ባፈሰስሽው ደም ላይ እጄን አጨበጭባለሁ። 14እኔ ልቀጣሽ በምነሣበት ጊዜ፣ በልበ ሙሉነት መቆም ትችያለሽን? ወይስ እጅሽ ሊበረታ ይችላልን? እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ፤ አደርገዋለሁም። 15በሕዝቦች መካከል እበትንሻለሁ፤ በየአገሩም እዘራሻለሁ፤ ከርኩሰትሽም አጠራሻለሁ። 16በሕዝቦች ዘንድ በምትረክሺበት ጊዜ፣22፥16 ወይም ርስትሽን ለአንቺ በሰጠሁሽ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቂያለሽ።’ ”

17የእግዚአብሔርም ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 18“የሰው ልጅ ሆይ፤ የእስራኤል ቤት የብረት ዝቃጭ ሆነብኝ፤ ሁሉም በከውር ውስጥ ቀልጦ እንደሚቀር መዳብ፣ ቈርቈሮ፣ ብረትና እርሳስ ናቸው፤ እነዚህ ከብር የሚወጡ ዝቃጭ ናቸው። 19ስለዚህ ልዑል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፣ ‘ሁላችሁም የብረት ዝቃጭ ስለ ሆናችሁ ወደ ኢየሩሳሌም እሰበስባችኋለሁ። 20ሰው ብርንና መዳብን፣ ብረትንና እርሳስን እንዲሁም ቈርቈሮን ለማቅለጥ በከውር ውስጥ አስገብቶ እሳት እንደሚያነድድበት፣ እኔም እንደዚሁ በቍጣዬና በመዓቴ ወደ ከተማዪቱ እሰበስባችኋለሁ፤ በዚያም አቀልጣችኋለሁ። 21ሰብስቤአችሁ የቍጣዬን እሳት በእስትንፋሴ አነድድባችኋለሁ፤ እናንተም በዚያ ውስጥ ቀልጣችሁ ትቀራላችሁ፤ እኔ እግዚአብሔር ቍጣዬን በላያችሁ እንዳፈሰስሁ ታውቃላችሁ። 22ብር በከውር ውስጥ እንደሚቀልጥ፣ እናንተም በከተማዋ ውስጥ ትቀልጣላችሁ፤ በዚያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር ቍጣዬን በላያችሁ እንዳፈሰስሁ ታውቃላችሁ።’ ”

23የእግዚአብሔርም ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 24“የሰው ልጅ ሆይ፤ ምድሪቱን፣ ‘አንቺ ያልነጻሽ በቍጣም ቀን ዝናብ ያላገኘሽ22፥24 ከሰብዐ ሊቃናት ጋር ተመሳሳይ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ያልነጻሽ ወይም ያልዘነበብሽ ይለዋል። ምድር ነሽ’ በላት። 25መሳፍንቷ22፥25 ከሰብዐ ሊቃናት ጋር ተመሳሳይ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ነቢያት ይለዋል እያገሣ ግዳዩን እንደሚቦጫጭቅ አንበሳ በውስጧ ያሤራሉ፤ ሕዝቡን ይበላሉ፤ ንብረትንና የከበሩ ነገሮችን ይነጥቃሉ፤ ብዙዎችንም ሴቶች መበለት ያደርጋሉ። 26ካህናቷ በሕጌ ላይ ያምፃሉ፤ ንዋያተ ቅድሳቴን ያረክሳሉ፤ የተቀደሰውን ከረከሰው አይለዩም፤ በጐደፈውና በንጹሑ መካከል ልዩነት እንደሌለ ያስተምራሉ፤ ሰንበታቴን ከማክበር ዘወር ብለዋል፤ በዚህም በመካከላቸው ተንቄአለሁ። 27በውስጧ የሚገኙ መኳንንቷ ግዳይ እንደሚቦጫጭቁ ተኵላዎች ናቸው፤ በግፍ ትርፍ ለመሰብሰብ ደም ያፈስሳሉ፤ ሕይወትም ያጠፋሉ። 28ነቢያቷም በሐሰት ራእይና በውሸት ሟርት ይህን ሁሉ ድርጊት ያድበሰብሱላቸዋል፤ እግዚአብሔርም ሳይናገር፣ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል’ ይላሉ። 29በምድሪቱ የሚኖረው ሕዝብ ይቀማል፤ ይዘርፋል፤ ፍትሕ በማጕደልም ድኻውንና ችግረኛውን ይጨቍናል፤ መጻተኛውንም ይበድላል።

30“ምድሪቱን እንዳላጠፋት ቅጥሩን የሚጠግን፣ በፈረሰውም በኩል በፊቴ የሚቆምላት ሰው ከመካከላቸው ፈለግሁ፤ ነገር ግን አንድም አላገኘሁም። 31ስለዚህ መዓቴን አፈስስባቸዋለሁ፤ በጽኑ ቍጣዬም አነድዳቸዋለሁ፤ ያደረጉትንም በራሳቸው ላይ እመልሳለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以西結書 22:1-31

耶路撒冷的罪惡

1耶和華對我說: 2「人子啊,你要審判耶路撒冷這殺人流血的城。你要審判她,使她知道自己一切可憎的行為。 3你要向她宣告主耶和華的話,說,『唉,你這殺人流血、製造偶像玷污自己的城啊,你的末日到了。 4你既犯罪殺人、製造偶像玷污自己、自招審判,我要使你成為列國列邦侮辱和譏諷的對象。 5你這聲名狼藉、混亂不堪的城將要受到遠近各國的恥笑。

6「『看啊,在你城中的以色列首領各逞權勢,殺人流血。 7他們輕慢父母,壓迫寄居者,欺負孤兒寡婦。 8他們藐視我的聖物,褻瀆我的安息日。 9在你這城中,有人好誹謗、殺人流血,有人在山上吃祭物,有人淫亂, 10有人與繼母通姦,羞辱父親,有人姦污經期不潔的婦女, 11有人與鄰居的妻子幹出可憎之事,有人玷污自己的兒媳婦,有人姦污自己的同父姊妹。 12在你這城中,他們受賄殺人,放債取利,壓榨鄰居,早把我忘了。這是主耶和華說的。

13「『我見你謀財害命,就擊掌歎息。 14在我懲罰你的日子,你還有勇氣和力量嗎?我耶和華言出必行, 15我要把你驅散到列國,分散到列邦,我要除掉你的污穢。 16你必在列國面前受凌辱,你便知道我是耶和華。』」

17耶和華對我說: 18「人子啊,在我看來,以色列人已經變成了渣滓。他們是爐中的銅、錫、鐵、鉛,都是銀渣滓。 19所以主耶和華說,『你們既是渣滓,我要把你們聚集在耶路撒冷城。 20我要在烈怒中把你們聚集在城裡熔化,就像人把銀、銅、鐵、鉛、錫聚在高溫的爐中熔化一樣。 21我要聚集你們,把我的怒火倒在你們身上,熔化你們。 22你們要在城中熔化,就像銀在煉爐中熔化。你們就知道我耶和華已將我的烈怒傾倒在你們身上。』」

23耶和華對我說: 24「人子啊,你要對以色列說,『在我發怒的日子,將沒有雨水滋潤你這不潔之地。 25你的首領圖謀惡事,好像咆哮著撕碎獵物的獅子,他們草菅人命,搶奪財寶,使多人變成寡婦。 26你的祭司強解我的律法,褻瀆我的聖物。他們聖俗不分,也不教導人分辨潔淨的和污穢的。他們藐視我的安息日,褻瀆我。 27你的首領好像撕碎獵物的豺狼,殺人流血,謀取不義之財。 28你的先知對他們說虛假的異象和占卜,像用白灰刷牆一樣掩蓋他們的罪惡,說,耶和華這樣說,其實耶和華沒有說。 29你的居民強取豪奪,欺壓貧困的,虐待寄居的,無法無天。 30我想在他們中間尋找一位重修城牆的人,站在我面前為這地方堵住缺口,免得我毀滅這裡。可是,我一個也找不到。 31因此,我要向他們傾倒我的烈怒,用怒火滅盡他們,照他們的所作所為報應他們。這是主耶和華說的。』」