ሐዋርያት ሥራ 8 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 8:1-40

1ሳውልም በእስጢፋኖስ መገደል ተስማምቶ ነበር።

የአማኞች መሰደድና መበተን

በዚያ ቀን በኢየሩሳሌም በነበረችው ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ተነሣ፤ ከሐዋርያትም በስተቀር አማኞች በሙሉ በይሁዳና በሰማርያ አውራጃዎች ሁሉ ተበተኑ፤ 2በመንፈሳዊ ነገር የተጉ ሰዎችም እስጢፋኖስን ቀበሩት፤ ደግሞም እጅግ አለቀሱለት። 3ሳውል ግን ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት ታጥቆ ተነሣ፤ ከቤት ወደ ቤት በመግባትም ወንዶችንና ሴቶችን ጐትቶ እያወጣ ወህኒ ቤት ያስገባቸው ነበር።

ፊልጶስ በሰማርያ

4የተበተኑትም በሄዱበት ሁሉ ቃሉን ሰበኩ፤ 5ፊልጶስም ወደ አንዲት የሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን8፥5 ወይም መሲሕ ሰበከላቸው። 6ብዙ ሕዝብም ፊልጶስ የተናገረውን ሲሰሙና ያደረገውንም ታምራዊ ምልክቶች ሲያዩ፣ አንድ ልብ ሆነው ያዳምጡት ነበር። 7ርኩሳን8፥7 ወይም ክፉ መናፍስትም እየጮኹ ከብዙ ሰዎች ወጡ፤ ብዙ ሽባዎችና ዐንካሶችም ተፈወሱ፤ 8ከዚህ የተነሣም በከተማዪቱ ታላቅ ደስታ ሆነ።

ጠንቋዩ ሲሞን

9ነገር ግን ከዚህ ቀደም ሲል በከተማዪቱ ውስጥ እየጠነቈለ የሰማርያን ሰዎች ሁሉ ያስገረመ፣ ሲሞን የሚሉት አንድ ሰው ነበር፤ እርሱም ራሱን እንደ ታላቅ ሰው ይቈጥር ነበር። 10ከታናሽ እስከ ታላቅ ያለው ሰው ሁሉ፣ “ይህ ሰው ‘ታላቁ ኀይል’ በመባል የሚታወቀው መለኮታዊ ኀይል ነው” በማለት ከልብ ያዳምጡት ነበር፤ 11ከብዙ ጊዜ ጀምሮ በጥንቈላ ሥራው ስላስገረማቸውም ትኵረት ሰጥተው ይከተሉት ነበር። 12ነገር ግን ፊልጶስ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም የሰበከላቸውን አምነው በመቀበላቸው ወንዶችም ሴቶችም ተጠመቁ፤ 13ራሱ ሲሞን እንኳ ሳይቀር አምኖ ተጠመቀ፤ ፊልጶስንም ተከትሎ ሄደ፤ የሚደረገውን ምልክትና ታላቅ ታምራት አይቶም ተገረመ።

14በኢየሩሳሌም የነበሩት ሐዋርያት የሰማርያ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል መቀበላቸውን በሰሙ ጊዜ፣ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ወደ እነርሱ ላኳቸው። 15እነርሱም ሰማርያ በደረሱ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን እንዲቀበሉ ለሰማርያ ሰዎች ጸለዩላቸው፤ 16ምክንያቱም በዚያን ጊዜ በጌታ ኢየሱስ ስም ተጠምቀው ነበር እንጂ ገና መንፈስ ቅዱስ በአንዳቸውም ላይ አልወረደም ነበር። 17ስለዚህ ጴጥሮስና ዮሐንስ እጃቸውን ጫኑባቸው፤ እነርሱም መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።

18ሲሞንም ሐዋርያት እጃቸውን በሚጭኑበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ እንደሚሰጥ አይቶ፣ ገንዘብ አመጣላቸውና እንዲህ አላቸው፤ 19“እጄን የምጭንበት ሰው ሁሉ መንፈስ ቅዱስን እንዲቀበል ይህን ሥልጣን ለእኔም ስጡኝ።”

20ጴጥሮስ ግን እንዲህ አለው፤ “የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ ለመግዛት አስበሃልና፣ አንተም ገንዘብህም አብራችሁ ጥፉ! 21ልብህ በእግዚአብሔር ፊት ቅን ስላልሆነ፣ አንተ በዚህ አገልግሎት ድርሻ ወይም ዕድል ፈንታ የለህም። 22አሁንም ስለዚህ ክፋትህ ንስሓ ግባ፤ ወደ ጌታም ጸልይ፤ ምናልባት ይህን የልብህን ሐሳብ ይቅር ይልህ ይሆናል፤ 23ምክንያቱም በመራራነት ተሞልተህ፣ በዐመፅ ሰንሰለት ተይዘህ አይሃለሁና።”

24ሲሞንም መልሶ፣ “ከተናገራችሁት ምንም ነገር እንዳይደርስብኝ ጌታን ለምኑልኝ” አላቸው።

25ጴጥሮስና ዮሐንስም የጌታን ቃል ከመሰከሩና ገልጠው ከተናገሩ በኋላ፣ በብዙ የሰማርያ መንደሮች ወንጌልን እየሰበኩ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።

ፊልጶስና ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ

26የጌታም መልአክ ፊልጶስን፣ “ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚያወርደው በምድረ በዳው መንገድ ሂድ” አለው፤ 27እርሱም ተነሥቶ ሄደ። እነሆ፤ የኢትዮጵያ ንግሥት የህንደኬ ባለሟልና የሀብት ንብረቷ ሁሉ አዛዥ የሆነ አንድ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ አገኘ። ይህም ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር። 28ሲመለስም በሠረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብብ ነበር። 29መንፈስም ፊልጶስን፣ “ሂድ፤ ወደዚህ ሠረገላ ቅረብ” አለው።

30ፊልጶስም ፈጥኖ ወደ ሠረገላው ሄደ፤ ጃንደረባውም የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብብ ሰምቶ፣ “ለመሆኑ፣ የምታነብበውን ታስተውለዋለህን?” አለው።

31ጃንደረባውም፣ “የሚያስረዳኝ ሰው ሳይኖር እንዴት አድርጌ አስተውላለሁ” አለው፤ እርሱም ወደ ሠረገላው ወጥቶ አብሮት እንዲቀመጥ ፊልጶስን ለመነው።

32ጃንደረባው ያነብብ የነበረው የመጽሐፍ ክፍል ይህ ነበር፤

“እንደ በግ ወደ መታረድ ተነዳ፤

የበግ ጠቦት በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል፣

እንዲሁ አፉን አልከፈተም።

33ራሱን በማዋረዱም ፍትሕን ተነፈገ፤

ሕይወቱ ከምድር ተወግዳለችና፣

ስለ ትውልዱ ማን ሊናገር ይችላል?”

34ጃንደረባውም መልሶ ፊልጶስን፣ “ነቢዩ ይህን የሚናገረው ስለ ማን ነው? ስለ ራሱ ነው ወይስ ስለ ሌላ ሰው? እባክህ ንገረኝ” አለው። 35ፊልጶስም አፉን ከፈተ፤ ከዚሁም መጽሐፍ ክፍል ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌል ሰበከለት።

36በመጓዝ ላይ ሳሉም ውሃ ካለበት ስፍራ ደረሱ፤ ጃንደረባውም፣ “እነሆ፤ ውሃ እዚህ አለ፤ ታዲያ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምን ነገር አለ?” አለው።

37ፊልጶስም፣ “በፍጹም ልብህ ካመንህ መጠመቅ ትችላለህ” አለው።

ጃንደረባውም፣ “ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ” ሲል መለሰለት፤8፥37 አንዳንድ የጥንት ቅጆች ይህ ጥቅስ የላቸውም። 38ሠረገላውም እንዲቆም አዘዘ። ከዚያም ሁለቱ አብረው ወደ ውሃው ወረዱ፤ ፊልጶስም ጃንደረባውን አጠመቀው። 39ከውሃውም በወጡ ጊዜ፣ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጥቆ ወሰደው፤ ጃንደረባውም ከዚህ በኋላ አላየውም፤ ሆኖም ደስ እያለው ጕዞውን ቀጠለ። 40ከዚያ በኋላ ግን ፊልጶስ በአዛጦን ታየ፤ ቂሳርያም እስኪደርስ ድረስ በሚያልፍባቸው ከተሞች ሁሉ ወንጌልን ይሰብክ ነበር።

New International Reader’s Version

Acts 8:1-40

1And Saul had agreed with the Sanhedrin that Stephen should die.

The Church Is Treated Badly and Scattered

On that day the church in Jerusalem began to be attacked and treated badly. All except the apostles were scattered throughout Judea and Samaria. 2Godly Jews buried Stephen. They mourned deeply for him. 3But Saul began to destroy the church. He went from house to house. He dragged away men and women and put them in prison.

Philip Goes to Samaria

4The believers who had been scattered preached the word everywhere they went. 5Philip went down to a city in Samaria. There he preached about the Messiah. 6The crowds listened to Philip and saw the signs he did. All of them paid close attention to what he said. 7Evil spirits screamed and came out of many people. Many people who were disabled or who couldn’t walk were healed. 8So there was great joy in that city.

Simon the Evil Magician

9A man named Simon lived in the city. For quite a while he had practiced evil magic there. He amazed all the people of Samaria. He claimed to be someone great. 10And all the people listened to him, from the least important of them to the most important. They exclaimed, “It is right to call this man the Great Power of God!” 11He had amazed them for a long time with his evil magic. So they followed him. 12But Philip announced the good news of God’s kingdom and the name of Jesus Christ. So men and women believed and were baptized. 13Simon himself believed and was baptized. He followed Philip everywhere. He was amazed by the great signs and miracles he saw.

14The apostles in Jerusalem heard that people in Samaria had accepted God’s word. So they sent Peter and John to Samaria. 15When they arrived there, they prayed for the new believers. They prayed that they would receive the Holy Spirit. 16The Holy Spirit had not yet come on any of them. They had only been baptized in the name of the Lord Jesus. 17Then Peter and John placed their hands on them. And they received the Holy Spirit.

18Simon watched as the apostles placed their hands on them. He saw that the Spirit was given to them. So he offered money to Peter and John. 19He said, “Give me this power too. Then everyone I place my hands on will receive the Holy Spirit.”

20Peter answered, “May your money be destroyed with you! Do you think you can buy God’s gift with money? 21You have no part or share in this holy work. Your heart is not right with God. 22Turn away from this evil sin of yours. Pray to the Lord. Perhaps he will forgive you for having such a thought in your heart. 23I see that you are very bitter. You are a prisoner of sin.”

24Then Simon answered, “Pray to the Lord for me. Pray that nothing you have said will happen to me.”

25Peter and John continued to preach the word of the Lord and tell people about Jesus. Then they returned to Jerusalem. On the way they preached the good news in many villages in Samaria.

Philip and the Man From Ethiopia

26An angel of the Lord spoke to Philip. “Go south to the desert road,” he said. “It’s the road that goes down from Jerusalem to Gaza.” 27So Philip started out. On his way he met an Ethiopian official. The man had an important position in charge of all the wealth of the Kandake. Kandake means queen of Ethiopia. This official had gone to Jerusalem to worship. 28On his way home he was sitting in his chariot. He was reading the Book of Isaiah the prophet. 29The Holy Spirit told Philip, “Go to that chariot. Stay near it.”

30So Philip ran up to the chariot. He heard the man reading Isaiah the prophet. “Do you understand what you’re reading?” Philip asked.

31“How can I?” he said. “I need someone to explain it to me.” So he invited Philip to come up and sit with him.

32Here is the part of Scripture the official was reading. It says,

“He was led like a sheep to be killed.

Just as lambs are silent while their wool is being cut off,

he did not open his mouth.

33When he was treated badly, he was refused a fair trial.

Who can say anything about his children?

His life was cut off from the earth.” (Isaiah 53:7,8)

34The official said to Philip, “Tell me, please. Who is the prophet talking about? Himself, or someone else?” 35Then Philip began with that same part of Scripture. He told him the good news about Jesus.

36-37As they traveled along the road, they came to some water. The official said, “Look! Here is water! What can stop me from being baptized?” 38He gave orders to stop the chariot. Then both Philip and the official went down into the water. Philip baptized him. 39When they came up out of the water, the Spirit of the Lord suddenly took Philip away. The official did not see him again. He went on his way full of joy. 40Philip was seen next at Azotus. From there he traveled all around. He preached the good news in all the towns. Finally he arrived in Caesarea.