ሉቃስ 22 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ሉቃስ 22:1-71

ይሁዳ ጌታን አሳልፎ ለመስጠት ተስማማ

22፥12 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥2-5ማር 14፥121011

1በዚህ ጊዜ ፋሲካ የተባለው የቂጣ በዓል ተቃርቦ ነበር። 2የካህናት አለቆችና ጸሐፍትም ሕዝቡን ይፈሩ ስለ ነበር፣ እንዴት አድርገው ኢየሱስን እንደሚያስወግዱት መንገድ ይፈልጉ ነበር። 3ሰይጣንም ከዐሥራ ሁለቱ ጋር በተቈጠረው የአስቆሮቱ ይሁዳ በተባለው ገባበት፤ 4ይሁዳም ወደ ካህናት አለቆችና ወደ ቤተ መቅደሱ ሹሞች ሄዶ ኢየሱስን እንዴት አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ተነጋገረ። 5እነርሱም በዚህ ደስ ተሰኝተው፣ ገንዘብ ሊሰጡት ተዋዋሉ። 6እርሱም በነገሩ ተስማማ፤ አሳልፎ ሊሰጣቸውም ሕዝብ የማይገኝበትን ምቹ ጊዜ ይጠብቅ ጀመር።

የመጨረሻው እራት

22፥7-13 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥17-19ማር 14፥12-16

22፥17-20 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥26-29ማር 14፥22-251ቆሮ 11፥23-25

22፥21-23 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥21-24ማር 14፥18-21ዮሐ 13፥21-30

22፥25-27 ተጓ ምብ – ማቴ 20፥25-28ማር 10፥42-45

22፥3334 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥33-35ማር 14፥29-31ዮሐ 13፥3738

7ከዚህ በኋላ የፋሲካ በግ የሚታረድበት የቂጣ በዓል ደረሰ። 8ኢየሱስም፣ “የፋሲካን እራት እንድንበላ ሄዳችሁ አዘጋጁልን” ብሎ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ላካቸው።

9እነርሱም፣ “የት እንድናሰናዳ ትፈልጋለህ?” አሉት።

10እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “እነሆ፤ ወደ ከተማ ስትገቡ የውሃ እንስራ የተሸከመ ሰው ያገኛችኋል፤ እርሱ ወደሚገባበት ቤት ድረስ ተከተሉት፤ 11ለቤቱም ባለቤት፣ ‘መምህሩ፣ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር የፋሲካን እራት የምበላበት የእንግዳ ክፍል ወዴት ነው? ይልሃል’ በሉት። 12እርሱም በሰገነት ላይ ያለውን ተነጥፎ የተዘጋጀ ሰፊ አዳራሽ ያሳያችኋል፤ በዚያም አሰናዱልን።”

13እነርሱም ሄደው ልክ ኢየሱስ እንደ ነገራቸው ሆኖ አገኙት፤ ፋሲካንም በዚያ አዘጋጁ።

14ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ኢየሱስ ከሐዋርያቱ ጋር በማእድ ተቀመጠ፤ 15እንዲህም አላቸው፤ “መከራ ከመቀበሌ በፊት ይህን ፋሲካ አብሬያችሁ ለመብላት በጣም ስመኝ ነበር፤ 16እላችኋለሁ፤ በእግዚአብሔር መንግሥት የዚህ ትርጕም እስኪፈጸም ድረስ ይህን ፋሲካ ዳግመኛ አልበላም።”

17ጽዋውን ተቀብሎ ካመሰገነ በኋላ እንዲህ አላቸው፤ “ዕንካችሁ፤ ሁላችሁ ከዚህ ተካፈሉ፤ 18እላችኋለሁና፤ ከአሁን ጀምሮ የእግዚአብሔር መንግሥት እስከምትመጣ ድረስ ከዚህ ወይን ፍሬ አልጠጣም።”

19እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ፤ ቈርሶም ሰጣቸውና፣ “ይህ ስለ እናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት” አለ።

20እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ፤ “ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈስሰው ደሜ የሚመሠረት አዲስ ኪዳን ነው። 21ነገር ግን አሳልፎ የሚሰጠኝ ሰው እጅ በማእድ ከእኔ ጋር ናት። 22የሰው ልጅስ አስቀድሞ በተወሰነው መሠረት ይሄዳል፤ ነገር ግን እርሱን አሳልፎ ለሚሰጠው ለዚያ ሰው ወዮለት።” 23እነርሱም ከመካከላቸው ይህን የሚያደርግ ማን ሊሆን እንደሚችል እርስ በርሳቸው ይጠያየቁ ጀመር።

24ደግሞም ከመካከላቸው ማን እንደሚበልጥ በእነርሱ ዘንድ ክርክር ተነሣ። 25ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “የአሕዛብ ነገሥታት ሕዝቦቻቸውን በኀይል ይገዛሉ፤ በእነርሱ ላይ ሥልጣን ያላቸውም በጎ አድራጊዎች ተብለው ይጠራሉ። 26በእናንተ ዘንድ ግን እንዲህ አይሁን፤ ይልቁን ከእናንተ ታላቅ የሆነ እንደ ታናሽ፣ ገዥ የሆነም እንደ አገልጋይ ይሁን። 27ለመሆኑ፣ በማእድ ከተቀመጠና ቆሞ ከሚያስተናግድ ማን ይበልጣል? በማእድ የተቀመጠው አይደለምን? እኔ ግን በመካከላችሁ ያለሁት እንደ አንድ አገልጋይ ነው። 28እናንተም ሳትለዩኝ በመከራዬ ጊዜ በአጠገቤ የቆማችሁ ናችሁ፤ 29አባቴ እኔን እንደ ሾመኝ እኔም ደግሞ በመንግሥቴ እሾማችኋለሁ፤ 30ይኸውም በመንግሥቴ ከማእዴ እንድትበሉና እንድትጠጡ ደግሞም በዙፋን ላይ ተቀምጣችሁ በዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ላይ እንድትፈርዱ ነው።”

31ደግሞም ኢየሱስ እንዲህ አለ፤ “ስምዖን፣ ስምዖን ሆይ፤ እነሆ፤ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤ 32እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ ጸለይሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አበርታ።”

33ስምዖንም፣ “ጌታ ሆይ፤ እኔ ከአንተ ጋር ወህኒ ለመውረድም፣ ለመሞትም ዝግጁ ነኝ” አለው።

34ኢየሱስም፣ “ጴጥሮስ ሆይ፤ እልሃለሁ፤ ዛሬ ዶሮ ሳይጮኽ፣ አላውቀውም ብለህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ” አለው።

35ከዚያም ኢየሱስ፣ “ያለ ኰረጆ፣ ያለ ከረጢትና ያለ ጫማ በላክኋችሁ ጊዜ የጐደለባችሁ ነገር ነበርን?” ብሎ ጠየቃቸው።

እነርሱም፣ “ምንም አልጐደለብንም” አሉ።

36እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “አሁን ግን ኰረጆም፣ ከረጢትም ያለው ሰው ይያዝ፤ ሰይፍ የሌለውም ልብሱን ሽጦ ይግዛ። 37እላችኋለሁና፤ ‘ከዐመፀኞች ጋር ተቈጠረ’ ተብሎ የተጻፈው በእኔ መፈጸም አለበት፤ ስለ እኔ የተጻፈው ፍጻሜው በርግጥ ደርሷል።”

38ደቀ መዛሙርቱም፣ “ጌታ ሆይ፤ እነሆ፤ ሁለት ሰይፎች እዚህ አሉ” አሉት።

እርሱም፣ “ይበቃል” አላቸው።

ኢየሱስ በደብረ ዘይት ተራራ ጸለየ

22፥40-46 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥36-46ማር 14፥32-42

39ኢየሱስ እንደ ልማዱ ወጥቶ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ሄደ፤ ደቀ መዛሙርቱም ተከተሉት። 40እዚያም በደረሱ ጊዜ፣ “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ” አላቸው። 41ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ ያህል ርቆ ተንበርክኮ ጸለየ፤ 42እንዲህም አለ፤ “አባት ሆይ፤ ፈቃድህ ከሆነ፣ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ ሳይሆን የአንተ ፈቃድ ይፈጸም።” 43መልአክም ከሰማይ ተገልጦለት አበረታታው። 44እጅግ ተጨንቆም በብርቱ ይጸልይ ነበር፤ ላቡም እንደ ደም ነጠብጣብ ወደ ምድር22፥44 አንዳንድ የጥንት ቅጆች ቍጥር 43 እና 44 የላቸውም። ይፈስስ ነበር።

45ከጸሎትም ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣ፤ እነርሱም ከሐዘን የተነሣ ተኝተው አገኛቸውና፣ 46“ለምን ትተኛላችሁ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ” አላቸው።

ኢየሱስ ተያዘ

22፥47-53 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥47-56ማር 14፥43-50ዮሐ 18፥3-11

47እርሱም ገና እየተነጋገረ ሳለ፣ ብዙ ሰዎች መጡ፤ ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ ይሁዳ የተባለውም ሰው ይመራቸው ነበር፤ ሊስመውም ወደ ኢየሱስ ተጠጋ። 48ኢየሱስ ግን፣ “ይሁዳ ሆይ፤ የሰውን ልጅ በመሳም አሳልፈህ ትሰጣለህን?” አለው።

49በኢየሱስ ዙሪያ የነበሩ ሰዎችም ሁኔታውን ተመልክተው “ጌታ ሆይ፤ በሰይፍ እንምታቸውን?” አሉት። 50ከእነርሱም አንዱ የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠው።

51ኢየሱስ ግን፣ “ተው! እዚህ ድረስም ፍቀዱ” አለ፤ የሰውየውንም ጆሮ ዳስሶ ፈወሰው።

52ከዚያም ኢየሱስ ሊይዙት የመጡትን የካህናት አለቆች፣ የቤተ መቅደስ ሹሞችና ሽማግሌዎችን እንዲህ አላቸው፤ “ወንበዴ እንደሚይዝ ሰው፣ ሰይፍና ቈመጥ ይዛችሁ ወጣችሁን? 53በየዕለቱ በቤተ መቅደስ ከእናንተ ጋር በነበርሁ ጊዜ እጃችሁን አላነሣችሁብኝም፤ ይህ ግን ጨለማ የነገሠበት ጊዜያችሁ ነው።”

ጴጥሮስ ኢየሱስን ካደ

22፥55-62 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥69-75ማር 14፥66-72ዮሐ 18፥16-1825-27

54ከዚህ በኋላ ኢየሱስን ይዘው ወሰዱት፤ ወደ ሊቀ ካህናቱም ግቢ አስገቡት፤ ጴጥሮስም በርቀት ይከተለው ነበር። 55ሰዎቹ በሊቀ ካህናቱ ግቢ ውስጥ እሳት አንድደው በአንድነት ተቀምጠው ሳለ፣ ጴጥሮስም ከእነርሱ ጋር ተቀምጦ ነበር። 56አንዲት የቤት ሠራተኛም ጴጥሮስ እሳቱ አጠገብ ተቀምጦ አየችውና ትኵር ብላ በመመልከት፣ “ይህ ሰው ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ” አለች።

57እርሱ ግን፣ “አንቺ ሴት፤ እኔ ዐላውቀውም” ብሎ ካደ።

58ከጥቂት ጊዜ በኋላም አንድ ሌላ ሰው አይቶት፣ “አንተም ደግሞ ከእነርሱ አንዱ ነህ” አለው።

ጴጥሮስ ግን፣ “አንተ ሰው፤ እኔ አይደለሁም” አለ።

59አንድ ሰዓት ያህል ቈይቶም፣ ሌላ ሰው በርግጠኝነት፣ “ይህ ሰው ከገሊላ ስለሆነ ያለ ጥርጥር ከእርሱ ጋር ነበረ” አለ።

60ጴጥሮስ ግን፣ “አንተ ሰው፤ የምትለውን እኔ አላውቅም” አለ፤ ይህንም ተናግሮ ገና ሳይጨርስ ዶሮ ጮኸ። 61ጌታም መለስ ብሎ ጴጥሮስን ተመለከተው፤ ጴጥሮስም፣ “ዛሬ ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ” ብሎ ጌታ የተናገረው ቃል ትዝ አለው። 62ጴጥሮስም ወደ ውጭ ወጥቶ ምርር ብሎ አለቀሰ።

ወታደሮች በኢየሱስ ላይ አፌዙበት

22፥63-65 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥6768ማር 14፥65ዮሐ 18፥2223

63ኢየሱስን አስረው ይጠብቁት የነበሩት ሰዎችም ያፌዙበትና ይመቱት ጀመር፤ 64ዐይኑንም ሸፍነው፣ “እስቲ ትንቢት ተናገር፤ የመታህ ማነው?” እያሉ ይጠይቁት ነበር። 65ሌላም ብዙ የስድብ ቃል እየተናገሩ ያቃልሉት ነበር።

ኢየሱስ በጲላጦስና በሄሮድስ ፊት

22፥67-71 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥63-66ማር 14፥61-63ዮሐ 18፥19-21

23፥23 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥11-14ማር 15፥2-5ዮሐ 18፥29-37

23፥18-25 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥15-26ማር 15፥6-15ዮሐ 18፥39–19፥16

66በነጋም ጊዜ፣ የሕዝብ ሽማግሌዎች፣ የካህናት አለቆችና ጸሐፍት ተሰበሰቡ፤ ኢየሱስንም በሸንጓቸው ፊት አቀረቡት። 67እነርሱም፣ “አንተ ክርስቶስ22፥67 ወይም መሲሕ ነህን? እስቲ ንገረን” አሉት።

ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “ብነግራችሁ አታምኑኝም፤ 68ብጠይቃችሁም አትመልሱም። 69ነገር ግን ከአሁን ጀምሮ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ኀይል ቀኝ ይቀመጣል።”

70በዚህ ጊዜ ሁሉም፣ “ታዲያ፣ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህን?” አሉት።

እርሱም፣ “መሆኔን እኮ እናንተው ተናገራችሁት” አላቸው።

71እነርሱም፣ “ከእንግዲህ ሌላ ምስክር ምን ያስፈልገናል? ራሳችን ከገዛ አንደበቱ ሰምተናልና” አሉ።

New International Version – UK

Luke 22:1-71

Judas agrees to betray Jesus

1Now the Festival of Unleavened Bread, called the Passover, was approaching, 2and the chief priests and the teachers of the law were looking for some way to get rid of Jesus, for they were afraid of the people. 3Then Satan entered Judas, called Iscariot, one of the Twelve. 4And Judas went to the chief priests and the officers of the temple guard and discussed with them how he might betray Jesus. 5They were delighted and agreed to give him money. 6He consented, and watched for an opportunity to hand Jesus over to them when no crowd was present.

The Last Supper

7Then came the day of Unleavened Bread on which the Passover lamb had to be sacrificed. 8Jesus sent Peter and John, saying, ‘Go and make preparations for us to eat the Passover.’

9‘Where do you want us to prepare for it?’ they asked.

10He replied, ‘As you enter the city, a man carrying a jar of water will meet you. Follow him to the house that he enters, 11and say to the owner of the house, “The Teacher asks: where is the guest room, where I may eat the Passover with my disciples?” 12He will show you a large room upstairs, all furnished. Make preparations there.’

13They left and found things just as Jesus had told them. So they prepared the Passover.

14When the hour came, Jesus and his apostles reclined at the table. 15And he said to them, ‘I have eagerly desired to eat this Passover with you before I suffer. 16For I tell you, I will not eat it again until it finds fulfilment in the kingdom of God.’

17After taking the cup, he gave thanks and said, ‘Take this and divide it among you. 18For I tell you I will not drink again from the fruit of the vine until the kingdom of God comes.’

19And he took bread, gave thanks and broke it, and gave it to them, saying, ‘This is my body given for you; do this in remembrance of me.’

20In the same way, after the supper he took the cup, saying, ‘This cup is the new covenant in my blood, which is poured out for you.22:19,20 Some manuscripts do not have given for you… poured out for you. 21But the hand of him who is going to betray me is with mine on the table. 22The Son of Man will go as it has been decreed. But woe to that man who betrays him!’ 23They began to question among themselves which of them it might be who would do this.

24A dispute also arose among them as to which of them was considered to be greatest. 25Jesus said to them, ‘The kings of the Gentiles lord it over them; and those who exercise authority over them call themselves Benefactors. 26But you are not to be like that. Instead, the greatest among you should be like the youngest, and the one who rules like the one who serves. 27For who is greater, the one who is at the table or the one who serves? Is it not the one who is at the table? But I am among you as one who serves. 28You are those who have stood by me in my trials. 29And I confer on you a kingdom, just as my Father conferred one on me, 30so that you may eat and drink at my table in my kingdom and sit on thrones, judging the twelve tribes of Israel.

31‘Simon, Simon, Satan has asked to sift all of you as wheat. 32But I have prayed for you, Simon, that your faith may not fail. And when you have turned back, strengthen your brothers.’

33But he replied, ‘Lord, I am ready to go with you to prison and to death.’

34Jesus answered, ‘I tell you, Peter, before the cock crows today, you will deny three times that you know me.’

35Then Jesus asked them, ‘When I sent you without purse, bag or sandals, did you lack anything?’

‘Nothing,’ they answered.

36He said to them, ‘But now if you have a purse, take it, and also a bag; and if you don’t have a sword, sell your cloak and buy one. 37It is written: “And he was numbered with the transgressors”22:37 Isaiah 53:12; and I tell you that this must be fulfilled in me. Yes, what is written about me is reaching its fulfilment.’

38The disciples said, ‘See, Lord, here are two swords.’

‘That’s enough!’ he replied.

Jesus prays on the Mount of Olives

39Jesus went out as usual to the Mount of Olives, and his disciples followed him. 40On reaching the place, he said to them, ‘Pray that you will not fall into temptation.’ 41He withdrew about a stone’s throw beyond them, knelt down and prayed, 42‘Father, if you are willing, take this cup from me; yet not my will, but yours be done.’ 43An angel from heaven appeared to him and strengthened him. 44And being in anguish, he prayed more earnestly, and his sweat was like drops of blood falling to the ground.22:43,44 Many early manuscripts do not have verses 43 and 44.

45When he rose from prayer and went back to the disciples, he found them asleep, exhausted from sorrow. 46‘Why are you sleeping?’ he asked them. ‘Get up and pray so that you will not fall into temptation.’

Jesus arrested

47While he was still speaking a crowd came up, and the man who was called Judas, one of the Twelve, was leading them. He approached Jesus to kiss him, 48but Jesus asked him, ‘Judas, are you betraying the Son of Man with a kiss?’

49When Jesus’ followers saw what was going to happen, they said, ‘Lord, should we strike with our swords?’ 50And one of them struck the servant of the high priest, cutting off his right ear.

51But Jesus answered, ‘No more of this!’ And he touched the man’s ear and healed him.

52Then Jesus said to the chief priests, the officers of the temple guard, and the elders, who had come for him, ‘Am I leading a rebellion, that you have come with swords and clubs? 53Every day I was with you in the temple courts, and you did not lay a hand on me. But this is your hour – when darkness reigns.’

Peter disowns Jesus

54Then seizing him, they led him away and took him into the house of the high priest. Peter followed at a distance. 55And when some there had kindled a fire in the middle of the courtyard and had sat down together, Peter sat down with them. 56A servant-girl saw him seated there in the firelight. She looked closely at him and said, ‘This man was with him.’

57But he denied it. ‘Woman, I don’t know him,’ he said.

58A little later someone else saw him and said, ‘You also are one of them.’

‘Man, I am not!’ Peter replied.

59About an hour later another asserted, ‘Certainly this fellow was with him, for he is a Galilean.’

60Peter replied, ‘Man, I don’t know what you’re talking about!’ Just as he was speaking, the cock crowed. 61The Lord turned and looked straight at Peter. Then Peter remembered the word the Lord had spoken to him: ‘Before the cock crows today, you will disown me three times.’ 62And he went outside and wept bitterly.

The guards mock Jesus

63The men who were guarding Jesus began mocking and beating him. 64They blindfolded him and demanded, ‘Prophesy! Who hit you?’ 65And they said many other insulting things to him.

Jesus before Pilate and Herod

66At daybreak the council of the elders of the people, both the chief priests and the teachers of the law, met together, and Jesus was led before them. 67‘If you are the Messiah,’ they said, ‘tell us.’

Jesus answered, ‘If I tell you, you will not believe me, 68and if I asked you, you would not answer. 69But from now on, the Son of Man will be seated at the right hand of the mighty God.’

70They all asked, ‘Are you then the Son of God?’

He replied, ‘You say that I am.’

71Then they said, ‘Why do we need any more testimony? We have heard it from his own lips.’