ሉቃስ 11 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሉቃስ 11:1-54

ኢየሱስ ያስተማረው ጸሎት

11፥2-4 ተጓ ምብ – ማቴ 6፥9-13

11፥9-13 ተጓ ምብ – ማቴ 7፥7-11

1አንድ ቀን ኢየሱስ በአንድ ስፍራ ይጸልይ ነበር፤ ጸሎቱንም እንደ ጨረሰ፣ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፣ “ጌታ ሆይ፤ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱን ጸሎት እንዳስተማራቸው አንተም መጸለይን አስተምረን” አለው።

2እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “ስትጸልዩ እንዲህ በሉ፤

“ ‘አባታችን11፥2 አንዳንድ ቅጆች በሰማይ የምትኖር አባታችን ይላሉ። ሆይ፤

ስምህ ይቀደስ፤

መንግሥትህ ትምጣ፤11፥2 አንዳንድ ቅጆች ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን ይላሉ።

3የዕለት እንጀራችንን በየዕለቱ ስጠን፤

4በደላችንን ይቅር በለን፤

እኛም የበደሉንን11፥4 አንዳንድ ቅጆች በእኛ ላይ ኀጢአት የሠሩትን ይላሉ። ሁሉ ይቅር ብለናልና።

ወደ ፈተናም አታግባን፤ ከክፉው አድነን እንጂ።’ ”11፥4 አንዳንድ ቅጆች ከክፉው አድነን እንጂ የሚለው የላቸውም።

5ደግሞም እንዲህ አላቸው፤ “ከእናንተ አንዱ ወዳጅ ቢኖረውና በእኩለ ሌሊት ወደ እርሱ ሄዶ፣ ‘ወዳጄ ሆይ፤ ሦስት እንጀራ አበድረኝ፤ 6አንድ ባልንጀራዬ ከመንገድ መጥቶብኝ የማቀርብለት ምንም ነገር የለኝምና’ ብሎ ለመነው እንበል።

7“በቤት ውስጥ ያለውም፣ ‘አታስቸግረኝ፤ በሩ ተቈልፏል፤ ልጆቼም አብረውኝ ተኝተዋል፤ ከእንግዲህ ተነሥቼ ልሰጥህ አልችልም’ ይለዋልን? 8እላችኋለሁ፤ ወዳጁ በመሆኑ ተነሥቶ ባይሰጠው እንኳ፣ ስለ ንዝነዛው11፥8 ወይም ስለ ብዙ ልመናው ብቻ የሚፈልገውን ሁሉ ይሰጠዋል።

9“ስለዚህ እላችኋለሁ፤ ለምኑ ይሰጣችኋል፤ ፈልጉ ታገኛላችሁ፤ በር አንኳኩ ይከፈትላችኋል፤ 10ምክንያቱም የሚለምን ሁሉ ይቀበላል፤ የሚፈልግም ያገኛል፤ በር ለሚያንኳኳም ይከፈትለታል።

11“ከእናንተ መካከል አባት ሆኖ ሳለ ልጁ11፥11 አንዳንድ ቅጆች ዳቦ ቢለምነው ድንጋይ የሚሰጠው አለን? የሚል አላቸው። ዓሣ ቢለምነው እባብ የሚሰጠው ይኖራልን? 12ወይስ ዕንቍላል ቢለምነው ጊንጥ ይሰጠዋልን? 13እናንተ ክፉዎች ሆናችሁ ሳላችሁ፣ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታን መስጠት ካወቃችሁበት፣ የሰማዩ አባታችሁ ታዲያ ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስን እንዴት አብልጦ አይሰጥ!”

ጌታ ኢየሱስና ብዔልዜቡል

11፥14-1517-2224-26 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥2224-2943-45

11፥17-22 ተጓ ምብ – ማር 3፥23-27

14አንድ ቀን ኢየሱስ ድዳ ጋኔን ያወጣ ነበር፤ ጋኔኑም ከወጣለት በኋላ ድዳው ሰው ተናገረ፤ ሕዝቡም ተገረመ። 15አንዳንዶቹ ግን፣ “በአጋንንት አለቃ፣ በብዔልዜቡል11፥15 ግሪኩ ብዔዜቡል ወይም ብዔል ዜብል ይላል፤ እንዲሁም 18፡19 ይመ፣ አጋንንትን ያወጣል” አሉ፤ 16አንዳንዶቹ ደግሞ ሊፈታተኑት ከሰማይ ምልክት እንዲያሳያቸው ከእርሱ ይፈልጉ ነበር።

17ኢየሱስ ግን ሐሳባቸውን ዐውቆ እንዲህ አላቸው፤ “እርስ በርሱ የሚከፋፈል መንግሥት ሁሉ ይጠፋል፤ የሚለያይ ቤትም ይወድቃል። 18ሰይጣንም እርስ በርሱ ከተከፋፈለ፣ መንግሥቱ እንዴት ይጸናል? አጋንንትን በብዔልዜቡል እንደማወጣ ትናገራላችሁና። 19እንግዲህ እኔ አጋንንትን የማወጣው በብዔልዜቡል ከሆነ፣ ልጆቻችሁ በማን ያወጧቸው ይሆን? ስለዚህ እነርሱ ፈራጆች ይሆኑባችኋል። 20እኔ ግን አጋንንትን የማወጣው በእግዚአብሔር ጣት ከሆነ፣ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ እንደ መጣች ዕወቁ።

21“ብርቱ ሰው በሚገባ ታጥቆ ቤቱን ከጠበቀ፣ ንብረቱ በሰላም ይቀመጣል። 22ነገር ግን ይበልጥ ብርቱ የሆነ ሰው መጥቶ ካጠቃውና ካሸነፈው ታምኖበት የነበረውን ትጥቁን ያስፈታዋል፤ ምርኮውንም ወስዶ ለሌሎች ያካፍላል።

23“ከእኔ ጋር ያልሆነ ይቃወመኛል፤ ከእኔ ጋር የማይሰበስብም ይበትናል።

24“ርኩስ11፥24 ወይም ክፉ መንፈስ ከሰው ሲወጣ ዕረፍት ፍለጋ ውሃ በሌለበት ስፍራ ይንከራተታል፤ ሳያገኝም ሲቀር፣ ‘ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ’ ይላል፤ 25ሲመለስም ቤቱ ተጠራርጐና ተስተካክሎ ያገኘዋል። 26ከዚያም በኋላ ሄዶ ሌሎች ከእርሱ የከፉ ሰባት አጋንንት ይዞ ይመጣል፤ ገብተውበትም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያ ሰው ከመጀመሪያው ይልቅ የኋለኛው ሁኔታ የከፋ ይሆንበታል።”

27ኢየሱስ ይህን እየተናገረ እያለ፣ ከሕዝቡ መካከል አንዲት ሴት ድምፅዋን ከፍ አድርጋ፣ “የተሸከመችህ ማሕፀንና የጠባሃቸው ጡቶች ብፁዓን ናቸው” አለችው።

28እርሱ ግን፣ “ብፁዓንስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚታዘዙት ናቸው” አለ።

የዮናስ ምልክትነት

11፥29-32 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥39-42

29ብዙ ሕዝብ እየተሰበሰበ በሄደ ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ ይል ጀመር፤ “ይህ ትውልድ ክፉ ነው፤ ታምራዊ ምልክት ይፈልጋል፤ ነገር ግን ከዮናስ ምልክት በስተቀር ሌላ አይሰጠውም። 30ምክንያቱም ዮናስ ለነነዌ ሰዎች ምልክት እንደ ሆናቸው የሰው ልጅም ለዚህ ትውልድ ምልክት ይሆናል። 31የደቡቧ ንግሥት በፍርድ ጊዜ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድባቸዋለች፤ እርሷ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳርቻ መጥታለችና፤ እነሆ፤ ከሰሎሞን የሚበልጥ እዚህ አለ። 32የነነዌ ሰዎችም በፍርድ ጊዜ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ እነርሱ የዮናስን ስብከት ሰምተው ንስሓ ገብተዋልና፤ እነሆ፣ ከዮናስ የሚበልጥ እዚህ አለ።

የሰውነት መብራት

11፥3435 ተጓ ምብ – ማቴ 6፥2223

33“መብራት አብርቶ በስውር ቦታ ወይም ከእንቅብ በታች የሚያስቀምጥ ማንም የለም፤ ይልቁን የሚገቡ ሰዎች ብርሃኑን እንዲያዩ በመቅረዝ ላይ ያስቀምጠዋል። 34የሰውነትህ ብርሃን ዐይንህ ናት፤ ዐይንህ ጤናማ ስትሆን መላ ሰውነትህ ብሩህ ይሆናል፤ ዐይንህ ታማሚ ከሆነች ግን መላ ሰውነትህ የጨለመ ይሆናል። 35ስለዚህ በውስጥህ ያለው ብርሃን ጨለማ እንዳይሆን ተጠንቀቅ። 36እንግዲህ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ከሆነና የጨለመ የሰውነት ክፍል ከሌለበት፣ የሰውነትህ ሁለንተና መብራት በወገግታው ያበራልህ ያህል ይደምቃል።”

ስድስት ዐይነት ወዮታ

37ኢየሱስ ንግግሩን እንደ ጨረሰ፣ አንድ ፈሪሳዊ ከእርሱ ጋር ምግብ እንዲበላ ጋበዘው፤ እርሱም አብሮት ገብቶ በማእድ ተቀመጠ። 38ፈሪሳዊውም ኢየሱስ ከምግብ በፊት እጁን እንዳልታጠበ ባየ ጊዜ ተደነቀ።

39ጌታም እንዲህ አለው፤ “አሁን እናንተ ፈሪሳውያን የጽዋውንና የወጭቱን ውጫዊ ክፍል ታጸዳላችሁ፤ ውስጣችሁ ግን በሥሥትና በክፋት የተሞላ ነው። 40እናንት ሞኞች፤ የውጭውን የፈጠረ የውስጡንም አልፈጠረምን? 41ነገር ግን በውስጥ ያለውን ምጽዋት11፥41 ወይም ያላችሁን አድርጋችሁ ስጡ፤ በዚህ ጊዜ ሁሉም ንጹሕ ይሆንላችኋል።

42“እናንት ፈሪሳውያን ግን ወዮላችሁ፤ ከአዝሙድና ከጤና አዳም እንዲሁም ከአትክልት ሁሉ ዐሥራት ታወጣላችሁ፤ ሆኖም ፍትሕንና እግዚአብሔርን መውደድ ቸል ትላላችሁ፤ ነገር ግን ያንን ሳትተዉ ይህኛውን ማድረግ በተገባችሁ ነበር።

43“እናንት ፈሪሳውያን ወዮላችሁ፤ በምኵራብ የክብር መቀመጫ፣ በገበያ መካከልም እጅ መነሣትን ትወድዳላችሁና።

44“ሰዎች ሳያውቁ በላዩ የሚሄዱበትን የተሰወረ መቃብር ስለምትመስሉ፣ ወዮላችሁ።”

45ከሕግ ዐዋቂዎች አንዱ መልሶ “መምህር ሆይ፤ እንዲህ ስትናገር እኮ እኛንም መስደብህ ነው” ሲል መለሰለት።

46ኢየሱስም እንዲህ አለ፤ “እናንት ሕግ ዐዋቂዎችም ደግሞ ወዮላችሁ፤ ሰዎች ሊሸከሙ የማይችሉትን ከባድ ሸክም ታሸክማላችሁ፤ እናንተ ራሳችሁ ግን በጣታችሁ እንኳ አትነኩትም።

47“አባቶቻችሁ የገደሏቸውን የነቢያትን መቃብር ስለምታበጃጁ፣ ወዮላችሁ፤ 48እንግዲህ የአባቶቻችሁን ሥራ የምታጸኑ ምስክሮች ናችሁ፤ እነርሱ ነቢያትን ገደሉ፤ እናንተም መቃብራቸውን ታበጃጃላችሁ። 49ስለዚህም የእግዚአብሔር ጥበብ እንዲህ አለች፤ ‘ነቢያትንና ሐዋርያትን እልክላቸዋለሁ፤ እነርሱ አንዳንዶቹን ይገድላሉ፤ ሌሎችንም ያሳድዳሉ።’ 50ስለዚህ ይህ ትውልድ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ስለ ፈሰሰው፣ ስለ ነቢያት ሁሉ ደም ተጠያቂ ነው፤ 51ከአቤል ደም ጀምሮ፣ በመሠዊያውና በቤተ መቅደሱ መካከል እስከ ፈሰሰው እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ ይፈለግበታል፤ አዎን፣ እላችኋለሁ፤ ይህ ትውልድ ለዚህ ተጠያቂ ነው።

52“እናንት ሕግ ዐዋቂዎች ወዮላችሁ፤ የዕውቀትን መክፈቻ ነጥቃችሁ ወስዳችኋልና፤ እናንተ ራሳችሁ አልገባችሁበትም፤ የሚገቡትንም ከልክላችኋል።”

53ኢየሱስ ከዚያ ከወጣ በኋላ፣ ጸሐፍትና ፈሪሳውያን ክፉኛ ይቃወሙትና በጥያቄም ያዋክቡት ጀመር፤ 54ከአፉ በሚወጣውም ቃል ሊያጠምዱት ያደቡ ነበር።

Thai New Contemporary Bible

ลูกา 11:1-54

คำสอนของพระเยซูเรื่องการอธิษฐาน

(มธ.6:9-13; 7:7-11)

1วันหนึ่งขณะพระเยซูทรงอธิษฐานอยู่ในที่แห่งหนึ่ง เมื่อพระองค์ทรงอธิษฐานจบ สาวกคนหนึ่งมาทูลว่า “พระองค์เจ้าข้า ขอทรงสอนพวกข้าพระองค์อธิษฐานเหมือนที่ยอห์นสอนสาวกของเขา”

2พระองค์จึงตรัสกับพวกเขาว่า “เมื่อพวกท่านอธิษฐาน จงทูลว่า

“ ‘ข้าแต่พระบิดา11:2 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าข้าแต่พระบิดาของข้าพระองค์ทั้งหลาย ผู้ทรงสถิตในสวรรค์

ขอให้พระนามของพระองค์เป็นที่เทิดทูนสักการะ

ขอให้อาณาจักรของพระองค์ได้รับการสถาปนาไว้11:2 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาเพิ่มข้อความว่าขอให้พระประสงค์ของพระองค์สำเร็จในโลกเช่นเดียวกับในสวรรค์

3ขอโปรดประทานอาหารประจำวันแก่ข้าพระองค์ทั้งหลาย

4ขอทรงอภัยบาปของข้าพระองค์ทั้งหลาย

เพราะข้าพระองค์ทั้งหลายอภัยให้ทุกคนที่ทำผิดบาปต่อข้าพระองค์ทั้งหลาย11:4 ภาษากรีกว่าทุกคนที่เป็นหนี้ข้าพระองค์ทั้งหลายเช่นกัน

และขออย่าให้ข้าพระองค์ทั้งหลายล้มลงเมื่อถูกทดลอง11:4 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าทดลอง แต่ขอทรงช่วยข้าพระองค์ทั้งหลายให้พ้นจากมารร้าย’ ”

5แล้วพระองค์ตรัสกับพวกเขาว่า “สมมุติว่าคนหนึ่งในพวกท่านมีเพื่อนมาหาตอนเที่ยงคืนและบอกว่า ‘เพื่อนเอ๋ย ขอยืมขนมปังสักสามก้อนเถิด 6เพราะมีเพื่อนคนหนึ่งเพิ่งเดินทางมาถึง และข้าพเจ้าไม่มีอะไรให้เขากิน’

7“แล้วคนที่อยู่ในบ้านก็ตอบว่า ‘อย่ามากวนใจเราเลย ประตูก็ปิดลงกลอนแล้ว และลูกๆ ของเราก็นอนอยู่กับเราบนเตียง เราลุกขึ้นไปหยิบอะไรให้ท่านไม่ได้หรอก’ 8เราบอกท่านว่า แม้เขาไม่ยอมลุกไปหยิบขนมปังให้เพราะเป็นเพื่อนกัน แต่เพราะกลัวขายหน้า11:8 หรือเพราะคนนั้นร้องขออย่างไม่ลดละ เขาก็จะลุกขึ้นไปหยิบทุกสิ่งให้ตามที่คนนั้นต้องการ

9“ฉะนั้นเราบอกท่านว่า จงขอแล้วท่านจะได้รับ จงหาแล้วท่านจะพบ จงเคาะแล้วประตูจะเปิดให้แก่ท่าน 10เพราะทุกคนที่ขอก็ได้รับ คนที่แสวงหาก็พบ และคนที่เคาะประตูก็จะเปิดให้แก่เขา

11“ใครบ้างในพวกท่านที่เป็นบิดา เมื่อบุตรขอ11:11 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าขอขนมปังก็เอาก้อนหินให้ หรือถ้าเขาขอปลาก็จะเอางูให้แทน? 12หรือถ้าเขาขอไข่ก็จะเอาแมงป่องให้? 13ถ้าแม้ท่านเองซึ่งเป็นคนชั่วยังรู้จักให้สิ่งดีๆ แก่บุตรของท่าน ยิ่งกว่านั้นสักเพียงใด พระบิดาของท่านในสวรรค์ย่อมประทานพระวิญญาณบริสุทธิ์แก่บรรดาผู้ที่ทูลขอพระองค์!”

พระเยซูกับเบเอลเซบุบ

(มธ.12:22,24-29,43-45; มก.3:23-27)

14พระเยซูทรงกำลังขับผีใบ้ เมื่อผีออกแล้วคนใบ้นั้นจึงพูดได้ ประชาชนก็เลื่อมใส 15แต่บางคนพูดว่า “คนนี้ขับผีออกโดยอาศัยเบเอลเซบุบ11:15 ภาษากรีกว่าเบเซบูลหรือเบเอลเซบูลเช่นเดียวกับข้อ 18,19เจ้าแห่งผี” 16บางคนก็ทดสอบพระองค์โดยขอหมายสำคัญจากฟ้าสวรรค์

17พระเยซูทรงทราบความคิดของพวกเขาและตรัสกับพวกเขาว่า “อาณาจักรใดๆ แตกแยกกันเองย่อมถูกทำลาย และครอบครัวไหนที่แตกแยกกันเองย่อมพังทลาย 18หากซาตานแตกแยกกับตัวเอง อาณาจักรของมันจะตั้งอยู่ได้อย่างไร? เราพูดเช่นนี้เพราะท่านว่าเราขับผีออกโดยเบเอลเซบุบ 19หากเราขับผีออกโดยเบเอลเซบุบ แล้วสาวกของพวกท่านเล่า ขับผีออกโดยอาศัยใคร? ฉะนั้นพวกเขาจะตัดสินท่าน 20แต่หากเราขับผีออกโดยนิ้วพระหัตถ์ของพระเจ้า อาณาจักรของพระเจ้าก็มาถึงพวกท่านแล้ว

21“เมื่อคนแข็งแรงถืออาวุธพร้อมและเฝ้าระวังบ้านของตน ทรัพย์สินของเขาก็ปลอดภัย 22แต่เมื่อคนที่แข็งแรงกว่าเข้ามาโจมตีและเอาชนะเขา ก็เอาอาวุธที่เจ้าของบ้านวางใจไปและแบ่งสิ่งของที่ยึดมาได้

23“ผู้ใดไม่อยู่ฝ่ายเราก็เป็นปฏิปักษ์กับเรา และผู้ใดไม่รวบรวมไว้กับเราก็ทำให้กระจัดกระจายไป

24“เมื่อวิญญาณชั่ว11:24 ภาษากรีกว่าโสโครกออกจากผู้ใดแล้ว มันก็ไปทั่วถิ่นแล้ง แสวงหาที่พักและไม่พบ มันจึงกล่าวว่า ‘ข้าจะกลับไปยังบ้านที่ข้าจากมา’ 25พอมาถึงก็พบว่าบ้านนั้นเก็บกวาดสะอาดและจัดเป็นระเบียบเรียบร้อย 26มันจึงไปพาผีอื่นๆ อีกเจ็ดตนซึ่งร้ายกว่ามันอีกเข้ามาอาศัยที่นั่น และในที่สุดสภาพของคนนั้นก็เลวร้ายยิ่งกว่าตอนแรกเสียอีก”

27ขณะพระเยซูกำลังตรัสสิ่งเหล่านี้อยู่ หญิงคนหนึ่งในฝูงชนก็ร้องขึ้นว่า “ความสุขมีแก่มารดาผู้ให้กำเนิดและเลี้ยงดูท่าน”

28พระองค์ตรัสตอบว่า “ความสุขมีแก่บรรดาผู้ได้ยินพระวจนะของพระเจ้าและเชื่อฟังต่างหาก”

หมายสำคัญของโยนาห์

(มธ.12:39-42)

29ขณะที่ฝูงชนหลั่งไหลมามากขึ้น พระเยซูตรัสว่า “คนในยุคนี้ชั่วช้า ขอแต่หมายสำคัญ แต่เขาจะไม่ได้รับหมายสำคัญอื่นยกเว้นหมายสำคัญของโยนาห์ 30เพราะโยนาห์เป็นหมายสำคัญแก่ชาวนีนะเวห์ฉันใด บุตรมนุษย์ก็เป็นหมายสำคัญแก่คนยุคนี้ฉันนั้น 31ในวันพิพากษา ราชินีแห่งแดนใต้จะลุกขึ้นพร้อมกับคนยุคนี้และกล่าวโทษพวกเขา เพราะพระนางมาจากสุดโลกเพื่อรับฟังสติปัญญาของโซโลมอน และบัดนี้ผู้11:31 หรือสิ่งเช่นเดียวกับข้อ 32ซึ่งยิ่งใหญ่กว่าโซโลมอนก็อยู่ที่นี่ 32ในวันพิพากษา ชาวนีนะเวห์จะยืนขึ้นพร้อมกับคนยุคนี้และกล่าวโทษพวกเขา เพราะชาวนีนะเวห์ได้กลับใจใหม่โดยคำเทศนาของโยนาห์ และบัดนี้ผู้ซึ่งยิ่งใหญ่กว่าโยนาห์ก็อยู่ที่นี่

ประทีปของกาย

(มธ.6:22,23)

33“ไม่มีใครจุดตะเกียงแล้ววางไว้ในที่ซ่อนเร้นหรือเอาฝาครอบ แต่ย่อมตั้งไว้บนเชิงตะเกียง เพื่อคนทั้งหลายที่เข้ามาจะเห็นแสงสว่าง 34ดวงตาของท่านคือประทีปของกาย หากตาของท่านดี กายของท่านทั้งกายก็จะเต็มไปด้วยความสว่าง แต่เมื่อตาของท่านเสีย กายของท่านก็จะเต็มไปด้วยความมืด 35ดังนั้น จงคอยดูอย่าให้ความสว่างในท่านกลับมืดมิด 36เพราะฉะนั้นถ้ากายของท่านทั้งกายเต็มไปด้วยความสว่าง และไม่มีส่วนใดมืด ทั้งกายของท่านก็จะสว่างไสวเหมือนเมื่อแสงตะเกียงส่องท่าน”

วิบัติหกประการ

37เมื่อพระเยซูตรัสจบ ฟาริสีคนหนึ่งเชิญพระองค์รับประทานอาหารกับเขา พระองค์จึงทรงเข้าไปนั่งรับประทานอาหารที่โต๊ะ 38แต่ฟาริสีคนนั้นสังเกตเห็นว่าพระองค์ไม่ได้ล้างพระหัตถ์ก่อนเสวยก็แปลกใจ

39แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับเขาว่า “เจ้าพวกฟาริสี ล้างถ้วยชามแต่ภายนอก แต่ภายในเต็มไปด้วยความโลภและความชั่วช้า 40เจ้าพวกคนเขลา! ผู้ที่สร้างข้างนอกก็สร้างข้างในด้วยไม่ใช่หรือ? 41แต่จงให้สิ่งที่มีอยู่ในชาม11:41 หรือสิ่งที่เจ้ามีอยู่แก่ผู้ยากไร้ แล้วทุกสิ่งจะสะอาดสำหรับพวกเจ้า

42“วิบัติแก่เจ้า พวกฟาริสี เจ้าถวายสิบลดของสะระแหน่ ขมิ้น และเครื่องเทศทั้งปวงของเจ้าแด่พระเจ้า แต่เจ้าละเลยความยุติธรรมและความรักของพระเจ้า เจ้าควรปฏิบัติอย่างหลังโดยไม่ละเลยอย่างแรก

43“วิบัติแก่เจ้า พวกฟาริสี เพราะเจ้าชอบที่นั่งที่สำคัญที่สุดในธรรมศาลา และชอบให้ผู้คนมาคำนับทักทายในย่านตลาด

44“วิบัติแก่เจ้า เพราะเจ้าเป็นเหมือนหลุมฝังศพที่ไม่ได้ทำเครื่องหมายไว้ ซึ่งผู้คนเดินย่ำโดยไม่รู้ว่าเป็นหลุมฝังศพ”

45ผู้เชี่ยวชาญทางบทบัญญัติคนหนึ่งทูลว่า “ท่านอาจารย์ ท่านพูดอย่างนี้ก็สบประมาทพวกเราด้วย”

46พระเยซูตรัสตอบว่า “และเจ้า พวกผู้เชี่ยวชาญทางบทบัญญัติ วิบัติแก่เจ้า เพราะเจ้าวางภาระหนักที่แบกแทบไม่ไหวให้ผู้คน ส่วนตัวเจ้าเองแม้แต่นิ้วๆ เดียวก็ไม่ขยับช่วยพวกเขา

47“วิบัติแก่เจ้าเพราะเจ้าสร้างอุโมงค์ฝังศพให้เหล่าผู้เผยพระวจนะ และบรรพบุรุษของเจ้าเองนั่นแหละที่ฆ่าพวกเขา 48ดังนั้นเจ้าพิสูจน์ให้เห็นว่าเจ้าเห็นชอบกับสิ่งที่บรรพบุรุษของตนทำไว้ พวกเขาเข่นฆ่าผู้เผยพระวจนะ ส่วนพวกเจ้าสร้างหลุมฝังศพให้ 49เพราะเหตุนี้พระเจ้าจึงตรัสโดยพระปัญญาของพระองค์ว่า ‘เราจะส่งผู้เผยพระวจนะและอัครทูตไปหาพวกเขา ซึ่งบางคนจะถูกพวกเขาฆ่า และบางคนจะถูกพวกเขาข่มเหง’ 50ฉะนั้นคนยุคนี้จะต้องรับผิดชอบโลหิตของผู้เผยพระวจนะทั้งปวงซึ่งหลั่งรินตั้งแต่แรกสร้างโลก 51คือจากโลหิตของอาแบลจนถึงโลหิตของเศคาริยาห์ผู้ถูกฆ่าระหว่างแท่นบูชากับสถานนมัสการ เราบอกท่านว่า คนยุคนี้จะต้องรับผิดชอบสิ่งนี้ทั้งหมด

52“วิบัติแก่เจ้า พวกผู้เชี่ยวชาญทางบทบัญญัติ เพราะเจ้าได้เอากุญแจแห่งความรู้ไป ตัวเจ้าเองไม่เข้าไป แล้วยังขัดขวางคนอื่นที่กำลังเข้าไป”

53เมื่อพระเยซูเสด็จไปจากที่นั่น พวกฟาริสีกับพวกธรรมาจารย์เริ่มต่อต้านพระองค์อย่างรุนแรง และเริ่มรุมกันตั้งคำถามใส่พระองค์ 54คอยจับผิดสิ่งที่พระองค์ตรัส