ሆሴዕ 4 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 4:1-19

በእስራኤል ላይ የቀረበ ክስ

1በምድሪቱ በምትኖሩ በእናንተ ላይ

እግዚአብሔር የሚያቀርበው ክስ ስላለው፣

እናንት እስራኤላውያን ይህን የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤

“ታማኝነት የለም፤ ፍቅርም የለም፤

እግዚአብሔርንም ማወቅ በምድሪቱ የለም።

2በዚያ ያለው ርግማን4፥2 መርገምን ያመለክታል፣ መዋሸት፣ መግደል፣

መስረቅና ማመንዘር ብቻ ነው፤

ቃል ኪዳንን ሁሉ ያፈርሳሉ፤

ደም ማፍሰስና ግድያ ይበዛል።

3ስለዚህ ምድሪቱ አለቀሰች፤4፥3 ወይም ደረቀች

በውስጧም የሚኖሩ ሁሉ ኰሰመኑ፤

የምድር አራዊት፣ የሰማይ ወፎች፣

የባሕርም ዓሦች ዐለቁ።

4“ነገር ግን ማንም ሰው አይከራከር፤

ማንም ሌላውን አይወንጅል፤

በካህናት ላይ ክስን እንደሚያቀርቡ፣

ሕዝብህ እንደዚያው ናቸውና።

5ቀንና ሌሊት ትደናበራላችሁ፤

ነቢያትም ከእናንተ ጋር ይደናበራሉ፤

ስለዚህ እናታችሁን አጠፋታለሁ፤

6ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቷል።

“ዕውቀትን ስለ ናቃችሁ፣

እኔም ካህናት እንዳትሆኑ ናቅኋችሁ፤

የአምላካችሁን ሕግ ስለ ረሳችሁ፣

እኔም ልጆቻችሁን እረሳለሁ።

7ካህናት በበዙ ቍጥር፣

በእኔ ላይ የሚያደርጉት ኀጢአት በዝቷል፤

ክብራቸውንም4፥7 ማሶሬቲክ የሚለው እንዲሁ ሲሆን የጥንት ዕብራውያን ጸሐፍት ትውፊት ግን ክብሬን ይላል። በውርደት ለውጠዋል።4፥7 ሱርስትና የጥንት ዕብራውያን ጸሐፍት ትውፊት የሚሉት እንዲሁ ሲሆን፣ ማሶሬቲክ ግን እለውጠዋለሁ ይላል።

8የሕዝቤ ኀጢአት ለመብል ሆኖላቸዋል፤

ርኩሰታቸውንም እጅግ ወደዱ።

9ካህናትም ከሕዝቡ የተለዩ አይደሉም፤

ሁሉንም እንደ መንገዳቸው እቀጣቸዋለሁ፤

እንደ ሥራቸውም እከፍላቸዋለሁ።

10“ይበላሉ ግን አይጠግቡም፤

ያመነዝራሉ ግን አይበዙም፤

እግዚአብሔርን በመተው፣

ራሳቸውን 11ለአመንዝራነት፣

ለአሮጌና ለአዲስ የወይን ጠጅ አሳልፈው ሰጡ፤

በእነዚህም የሕዝቤ ማስተዋል ተወሰደ፤

12ከዕንጨት የተሠራውን ጣዖት ምክር ይጠይቃሉ፤

ዘንጋቸውም ይመልስላቸዋል።

የአመንዝራነት መንፈስ ያስታቸዋል፤

ለአምላካቸውም ታማኝ አልሆኑም።

13በተራሮችም ጫፍ ላይ ይሠዋሉ፤

መልካም ጥላ ባለው፣ በባሉጥ፣

በኮምቦልና በአሆማ ዛፍ ሥር፣

በኰረብቶችም ላይ የሚቃጠል ቍርባን ያቀርባሉ።

ስለዚህ ሴቶች ልጆቻችሁ ዘማውያን፣

ምራቶቻችሁም አመንዝራዎች ይሆናሉ።

14“ሴቶች ልጆቻችሁ ዘማውያን ሲሆኑ፣

የልጆቻችሁም ሚስቶች ሲያመነዝሩ

አልቀጣቸውም።

ወንዶች ከጋለሞቶች ጋር ይሴስናሉ፤

ከቤተ ጣዖት ዘማውያን ጋር ይሠዋሉና፤

የማያስተውል ሕዝብ ወደ ጥፋት ይሄዳል!

15“እስራኤል ሆይ፤ አንቺ ብታመነዝሪም፣

ይሁዳ በበደለኛነት አትጠየቅ።

“ወደ ጌልገላ አትሂዱ፤

ወደ ቤትአዌንም4፥15 ቤትአዌን የእግዚአብሔር ቤት የተባለችው ቤቴል ስትሆን፣ የቃሉ ትርጕም የክፋት ቤት ማለት ነው። አትውጡ፤

‘ሕያው እግዚአብሔርን’ ብላችሁም አትማሉ።

16እስራኤላውያን እንደ እልኸኛ ጊደር፣

እልኸኞች ናቸው፤

ታዲያ እግዚአብሔር እነርሱን በመልካም መስክ ውስጥ እንዳሉ የበግ ጠቦቶች

እንዴት ያሰማራቸዋል?

17ኤፍሬም ከጣዖት ጋር ተጣምሯል፤

እስቲ ተዉት፤

18መጠጣቸው ባለቀ ጊዜ እንኳ፣

ዘማዊነታቸውን አያቆሙም፤

ገዦቻቸውም ነውርን አጥብቀው ይወድዳሉ።

19ዐውሎ ነፋስ ጠራርጎ ይወስዳቸዋል፤

መሥዋዕቶቻቸውም ኀፍረት ያመጡባቸዋል።”

Ketab El Hayat

هوشع 4:1-19

فجور بني إسرائيل

1اسْمَعُوا كَلِمَةَ الرَّبِّ يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ، لأَنَّ لِلرَّبِّ دَعْوَى عَلَى أَهْلِ الأَرْضِ إِذْ خَلَتِ الأَرْضُ مِنَ الأَمَانَةِ وَالإِحْسَانِ وَمَعْرِفَةِ اللهِ. 2وَتَفَشَّتْ فِيهَا اللَّعْنَةُ وَالْكَذِبُ وَالْقَتْلُ وَالسَّرِقَةُ وَالْفِسْقُ. قَدْ تَخَطَّوْا كُلَّ حَدٍّ، وَسَفْكُ الدَّمِ يَعْقُبُهُ سَفْكُ دَمٍ. 3لِذَلِكَ تَنُوحُ الأَرْضُ، وَيَذْوِي كُلُّ مُقِيمٍ فِيهَا، فَضْلاً عَنْ وَحْشِ الْبَرِّ وَطَيْرِ السَّمَاءِ، بَلْ سَمَكُ الْبَحْرِ يُسْتَأْصَلُ أَيْضاً.

4وَلَكِنْ لَا يُخَاصِمُ أَحَدٌ أَحَداً، وَلا يَتَّهِمُهُ لأَنَّ دَعْوَايَ هِي ضِدَّكُمْ أَيُّهَا الْكَهَنَةُ. 5إِنَّكَ تَتَعَثَّرُ فِي النَّهَارِ، وَيَكْبُو النَّبِيُّ مَعَكَ فِي اللَّيْلِ، وَأَنَا أُدَمِّرُ أُمَّكُمْ إِسْرَائِيلَ. 6قَدْ هَلَكَ شَعْبِي لافْتِقَارِهِ إِلَى الْمَعْرِفَةِ، وَلأَنَّكَ رَفَضْتَ الْمَعْرِفَةَ فَأَنَا أَرْفُضُكَ فَلا تَكُونُ لِي كَاهِناً، أَنْتَ تَجَاهَلْتَ شَرِيعَتِي لِذَلِكَ أَنَا أَنْسَى أَبْنَاءَكَ. 7وَبِقَدْرِ مَا تَكَاثَرُوا تَفَاقَمَتْ خَطِيئَتُهُمْ، لِذَلِكَ أُحَوِّلُ مَجْدَهُمْ إِلَى عَارٍ. 8يَأْكُلُونَ مِنْ ذَبَائِحِ خَطِيئَةِ شَعْبِي وَيَفْرَحُونَ لِتَمَادِيهِمْ فِي الإِثْمِ لِيَكْثُرَ نَصِيبُهُمْ مِنْهَا. 9فَيُصْبِحُ الشَّعْبُ كَالْكَاهِنِ. وَأُعَاقِبُهُمْ جَمِيعاً عَلَى سُوءِ تَصَرُّفَاتِهِمْ وَأَجْزِيهِمْ عَلَى أَعْمَالِهِمْ. 10فَيَأْكُلُونَ وَلا يَشْبَعُونَ، وَيَزْنُونَ وَلا يَتَكَاثَرُونَ، لأَنَّهُمْ نَبَذُوا الرَّبَّ وَاسْتَسْلَمُوا إِلَى الْعَهَارَةِ.

11قَدْ سَلَبَتِ الْخَمْرَةُ الْمُعَتَّقَةُ وَالْجَدِيدَةُ عُقُولَ شَعْبِي 12فَيَطْلُبُونَ مَشُورَةَ قِطْعَةِ خَشَبٍ وَيَسْأَلُونَ عَصاً! لأَنَّ رُوحَ زِنىً قَدْ أَضَلَّهُمْ فَنَبَذُوا إِلَهَهُمْ وَزَنَوْا وَرَاءَ آخَرَ. 13ذَبَحُوا عَلَى قِمَمِ الْجِبَالِ وَأَصْعَدُوا تَقْدِمَاتِهِمْ عَلَى التِّلالِ وَتَحْتَ شَجَرِ الْبَلُّوطِ وَاللُّبْنَى وَالْبُطْمِ لِطِيبِ ظِلِّهَا. لِذَلِكَ تَزْنِي بَنَاتُكُمْ وَتَفْسِقُ كَنَّاتُكُمْ.

14وَلَكِنِّي لَنْ أُعَاقِبَ بَنَاتِكُمْ حِينَ يَزْنِينَ، وَلا كَنَّاتِكُمْ حِينَ يَفْسِقْنَ لأَنَّ الرِّجَالَ أَنْفُسَهُمْ قَدْ تَوَرَّطُوا مَعَ الزَّانِيَاتِ، وَذَبَحُوا مُحَرَّمَاتٍ مَعَ بَغَايَا الْمَعَابِدِ الْوَثَنِيَّةِ، وَالشَّعْبُ غَيْرُ الْمُتَعَقِّلِ يَلْحَقُ بِهِ الدَّمَارُ.

15فَإِنْ كُنْتَ يَا شَعْبَ إِسْرَائِيلَ زَانِياً، فَلا تَجْعَلْ يَهُوذَا يَأْثَمُ أَوْ يَذْهَبُ إِلَى الْجِلْجَالِ أَوْ إِلَى بَيْتِ آوَنَ وَلا يَحْلِفُ قَائِلاً: حَيٌّ هُوَ الرَّبُّ. 16إِنَّ إِسْرَائِيلَ شَعْبٌ عَنِيدٌ كَعِجْلَةٍ جَامِحَةٍ، فَكَيْفَ يَرْعَاهُمُ الرَّبُّ كَحَمَلٍ فِي مَرْجٍ رَحْبٍ؟ 17إِنَّ أَفْرَايِمَ مُكَبَّلٌ بِعِبَادَةِ الأَصْنَامِ، فَاتْرُكُوهُ وَحِيداً. 18وَحَالَمَا يَنْضُبُ خَمْرُهُمْ يَنْغَمِسُونَ فِي فَسَادِهِمْ، مُفَضِّلِينَ الْعَارَ عَلَى الشَّرَفِ. 19قَدْ صَرَّتْهُمُ الرِّيحُ فِي أَجْنِحَتِهَا، وَأَنْزَلَتْ بِهِمْ ذَبَائِحُهُمُ الْوَثَنِيَّةُ الْعَارَ.