ሆሴዕ 13 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 13:1-16

የእግዚአብሔር ቍጣ በእስራኤል ላይ

1ኤፍሬም ሲናገር ሰዎች ተንቀጠቀጡ፤

በእስራኤልም የተከበረ ነበር፤

ነገር ግን በኣልን ስላመለከ በደለ፤ ሞተም።

2አሁንም ኀጢአትን መሥራት አበዙ፤

ብራቸውን አቅልጠው ለራሳቸው ጣዖት ሠሩ፣

በጥበብ የተሠሩ ምስሎችን አበጁ፤

ሁሉም የባለ እጅ ሥራ ናቸው።

ስለ እነዚህ ሰዎች እንዲህ ተብሏል፤

“ሰውን መሥዋዕት አድርገው ያቀርባሉ፤

የጥጃ ጣዖቶችንም ይስማሉ”13፥2 ወይም መሥዋዕት የሚያቀርቡ ሰዎች… ይስማሉ

3ስለዚህ እንደ ማለዳ ጉም፣

ፈጥኖ እንደሚጠፋ የጧት ጤዛ፣

ከዐውድማ እንደሚጠረግ እብቅ፣

በመስኮትም እንደሚወጣ ጢስ ይሆናሉ።

4“እኔ ግን ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ፣13፥4 ወይም በግብፅ ከነበራችሁበት ጊዜ አንሥቶ

አምላክህ እግዚአብሔር ነኝ፤

ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ አታውቅም፤

ከእኔም በቀር ሌላ አዳኝ የለም።

5በምድረ በዳ፣

በሐሩር ምድርም ተንከባከብሁህ።

6ካበላኋቸው በኋላ ጠገቡ፤

በጠገቡ ጊዜ ታበዩ፤

ከዚያም ረሱኝ።

7ስለዚህ እንደ አንበሳ እመጣባቸዋለሁ፤

እንደ ነብርም በመንገድ አደባባቸዋለሁ።

8ግልገሎቿን እንደ ተነጠቀች ድብ፣

እመታቸዋለሁ፤ እዘነጣጥላቸዋለሁ።

እንደ አንበሳም ሰልቅጬ እውጣቸዋለሁ፤

የዱር አራዊትም ይገነጣጥላቸዋል።

9“እስራኤል ሆይ፤ በእኔ ላይ ስለ ተነሣህ፣

ረዳትህንም ስለ ተቃወምህ ትጠፋለህ።

10‘ንጉሥንና አለቆችን ስጠኝ፤’

ብለህ እንደ ጠየቅኸው፣

ያድንህ ዘንድ ንጉሥህ የት አለ?

በከተሞችህ ሁሉ የነበሩ ገዦችህስ የት አሉ?

11በቍጣዬ ንጉሥን ሰጠሁህ፤

በመዓቴም ሻርሁት።

12የኤፍሬም በደል ተከማችቷል፤

ኀጢአቱም በመዝገብ ተይዟል።

13በምጥ ላይ እንዳለች ሴት ጭንቅ ይመጣበታል፤

እርሱ ግን ጥበብ የሌለው ልጅ ነው፤

የሚወለድበት ጊዜ ሲደርስ፣

ከእናቱ ማሕፀን መውጣት የማይፈልግ ሕፃን ነው።

14“ከመቃብር ኀይል እታደጋቸዋለሁ፤

ከሞትም እቤዣቸዋለሁ፤

ሞት ሆይ፤ መቅሠፍትህ የት አለ?

መቃብር ሆይ፤13፥14 በዕብራይስጥ ሲኦል ማለት ነው ማጥፋትህ የት አለ?

“ከእንግዲህ ወዲህ አልራራለትም፤

15በወንድሞቹ መካከል ቢበለጽግም እንኳ፣

የምሥራቅ ነፋስ ከምድረ በዳ እየነፈሰ፣

ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል፤

ምንጩ ይነጥፋል፤

የውሃ ጕድጓዱም ይደርቃል።

የከበረው ሀብቱ ሁሉ፣

ከግምጃ ቤቱ ይበዘበዛል።

16የሰማርያ ሰዎች በደላቸውን ይሸከማሉ፤

በአምላካቸው ላይ ዐምፀዋልና፤

በሰይፍ ይወድቃሉ፤

ሕፃኖቻቸውም በምድር ላይ ይፈጠፈጣሉ፤

የእርጉዝ ሴቶቻቸውም ሆድ ይቀደዳል።”

King James Version

Hosea 13:1-16

1When Ephraim spake trembling, he exalted himself in Israel; but when he offended in Baal, he died. 2And now they sin more and more, and have made them molten images of their silver, and idols according to their own understanding, all of it the work of the craftsmen: they say of them, Let the men that sacrifice kiss the calves.13.2 they sin…: Heb. they add to sin13.2 the men…: or, the sacrificers of men 3Therefore they shall be as the morning cloud, and as the early dew that passeth away, as the chaff that is driven with the whirlwind out of the floor, and as the smoke out of the chimney. 4Yet I am the LORD thy God from the land of Egypt, and thou shalt know no god but me: for there is no saviour beside me.

5¶ I did know thee in the wilderness, in the land of great drought.13.5 great…: Heb. droughts 6According to their pasture, so were they filled; they were filled, and their heart was exalted; therefore have they forgotten me. 7Therefore I will be unto them as a lion: as a leopard by the way will I observe them: 8I will meet them as a bear that is bereaved of her whelps, and will rend the caul of their heart, and there will I devour them like a lion: the wild beast shall tear them.13.8 wild…: Heb. beast of the field

9¶ O Israel, thou hast destroyed thyself; but in me is thine help.13.9 is…: Heb. in thy help 10I will be thy king: where is any other that may save thee in all thy cities? and thy judges of whom thou saidst, Give me a king and princes?13.10 I will…: rather, Where is thy king? 11I gave thee a king in mine anger, and took him away in my wrath. 12The iniquity of Ephraim is bound up; his sin is hid. 13The sorrows of a travailing woman shall come upon him: he is an unwise son; for he should not stay long in the place of the breaking forth of children.13.13 long: Heb. a time 14I will ransom them from the power of the grave; I will redeem them from death: O death, I will be thy plagues; O grave, I will be thy destruction: repentance shall be hid from mine eyes.13.14 power: Heb. hand

15¶ Though he be fruitful among his brethren, an east wind shall come, the wind of the LORD shall come up from the wilderness, and his spring shall become dry, and his fountain shall be dried up: he shall spoil the treasure of all pleasant vessels.13.15 pleasant…: Heb. vessels of desire 16Samaria shall become desolate; for she hath rebelled against her God: they shall fall by the sword: their infants shall be dashed in pieces, and their women with child shall be ripped up.