ሆሴዕ 11 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 11:1-12

የእግዚአብሔር ፍቅር ለእስራኤል

1“እስራኤል ገና ሕፃን ሳለ ወደድሁት፤

ልጄንም ከግብፅ ጠራሁት።

2እስራኤል ግን አብዝቼ በጠራኋቸው11፥2 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ቅጆች እንዲሁ ሲሆኑ፣ ዕብራይስጡ ግን በጠሯቸው ይላል። ቍጥር፣

አብዝተው ከእኔ11፥2 ሰብዐ ሊቃናት እንዲሁ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን ከእነርሱ ይላል። ራቁ፤

ለበኣል አማልክት ሠዉ፤

ለምስሎችም ዐጠኑ።

3ኤፍሬምን እጁን ይዤ፣

እንዲራመድ ያስተማርሁት እኔ ነበርሁ፤

ነገር ግን የፈወስኋቸው እኔ እንደ ሆንሁ፣

እነርሱ አላስተዋሉም።

4በሰው የርኅራኄ ገመድ፣

በፍቅርም ሰንሰለት ሳብኋቸው፤

ቀንበሩን ከጫንቃቸው ላይ አነሣሁላቸው፤

ዝቅ ብዬም መገብኋቸው።

5“ታዲያ ንስሓ መግባትን እንቢ በማለታቸው፣

ወደ ግብፅ አይመለሱምን?

አሦርስ አይገዛቸውምን?

6በከተሞቻቸው ላይ ሰይፍ ይመዘዛል፤

የበሮቻቸውን መወርወሪያ ይቈርጣል፤

ስለ ክፉ ዕቅዳቸውም ይደመስሳቸዋል።

7ሕዝቤ ከእኔ ዘወር ማለትን መረጡ፤

ወደ ልዑል ቢጣሩም፣

በምንም ዐይነት አያከብራቸውም።

8“ኤፍሬም ሆይ፤ እንዴት እጥልሃለሁ?

እስራኤል ሆይ፤ እንዴትስ አሳልፌ እሰጥሃለሁ?

እንዴት እንደ አዳማ አደርግሃለሁ?

እንዴትስ እንደ ሲባዮ እፈጽምብሃለሁ?

ልቤ በውስጤ ተናወጠ፤

ምሕረቴም ሁሉ ተነሣሥቷል።

9የቍጣዬን መቅሠፍት አላመጣም፤

ተመልሼም ኤፍሬምን አላጠፋም፤

እኔ በመካከላችሁ ያለሁ ቅዱስ አምላክ ነኝ እንጂ፣

ሰው አይደለሁምና፣

በቍጣ አልመጣም።11፥9 ወይም በማንኛውም ከተማ ላይ በተቃውሞ አልመጣም

10እግዚአብሔርን ይከተላሉ፤

እርሱም እንደ አንበሳ ያገሣል፤

እርሱ ሲያገሣ፣

ልጆቹ እየተንቀጠቀጡ ከምዕራብ ይመጣሉ።

11እንደ ወፍ ከግብፅ፣

እንደ ርግብ ከአሦር፣

እየበረሩ ይመጣሉ፤

እኔም በቤታቸው አኖራቸዋለሁ”

ይላል እግዚአብሔር

የእስራኤል ኀጢአት

12ኤፍሬም በሐሰት፣

የእስራኤልም ቤት በተንኰል ከበበኝ፤

ይሁዳ ለአምላክ የማይገዛ፣

የታመነውን ቅዱሱን የሚቃወም ነው።

Thai New Contemporary Bible

โฮเชยา 11:1-12

ความรักของพระเจ้าต่ออิสราเอล

1“เมื่ออิสราเอลยังเด็กอยู่ เรารักเขา

เราเรียกบุตรของเราออกจากอียิปต์

2แต่ยิ่งเรา11:2 ภาษาฮีบรูว่าพวกเขาเรียกอิสราเอลมากเท่าใด

พวกเขายิ่งไกลห่างจากเรา11:2 ภาษาฮีบรูว่าพวกเขามากเท่านั้น

พวกเขาถวายเครื่องบูชาแก่พระบาอัล

และเผาเครื่องหอมถวายรูปปั้นต่างๆ

3เรานี่แหละสอนให้เอฟราอิมหัดเดิน

เราโอบอุ้มพวกเขาไว้ในอ้อมแขน

แต่พวกเขาไม่ตระหนัก

ว่าเรานี่แหละเป็นผู้รักษาพวกเขาให้หาย

4เรานำพวกเขาด้วยสายใยแห่งความเมตตา

และด้วยพันธะแห่งความรัก

เราปลดแอกจากคอของพวกเขา

และก้มลงมาป้อนอาหารพวกเขา

5“พวกเขาจะไม่กลับไปยังอียิปต์หรือ

และอัสซีเรียจะไม่ปกครองพวกเขาหรือ

ในเมื่อพวกเขาไม่ยอมกลับใจ?

6ดาบทั้งหลายจะกวัดแกว่งอยู่ในเมืองต่างๆ ของพวกเขา

จะทำลายดาลประตูของพวกเขา

และทำให้แผนการต่างๆ ของพวกเขาจบสิ้นลง

7ประชากรของเราตั้งใจทิ้งเราไป

แม้ว่าพวกเขาจะร้องทูลต่อเราผู้สูงสุด

เราก็จะไม่เชิดชูพวกเขาเลย

8“เอฟราอิมเอ๋ย เราจะปล่อยเจ้าหลุดมือไปได้อย่างไร?

อิสราเอลเอ๋ย เราจะยอมปล่อยเจ้าไปได้อย่างไร?

เราจะปฏิบัติต่อเจ้าเหมือนอัดมาห์ได้หรือ?

เราจะทำให้เจ้าเหมือนเศโบยิมได้อย่างไร?

จิตใจที่อยู่ภายในเราก็เปลี่ยนไป

ความเมตตาเอ็นดูของเราก็ได้รับการปลุกขึ้น

9เราจะไม่ลงโทษเจ้าตามความโกรธอันรุนแรงของเรา

หรือหันมาทำลายล้างเอฟราอิมอีก

เพราะเราเป็นพระเจ้า ไม่ใช่มนุษย์

เป็นองค์บริสุทธิ์ท่ามกลางเจ้า

เราจะไม่มาด้วยความโกรธ11:9 หรือไม่มาต่อสู้กับเมืองใดๆ

10เขาจะติดตามองค์พระผู้เป็นเจ้า

พระองค์จะทรงเปล่งพระสุรเสียงดุจราชสีห์

เมื่อพระองค์ทรงเปล่งเสียงกึกก้อง

ลูกๆ ของพระองค์จะสั่นสะท้านกลับมาจากทางตะวันตก

11เขาจะรีบรุดตัวสั่น

มาจากอียิปต์เหมือนนก

และมาจากอัสซีเรียเหมือนนกพิราบ

เราจะพาพวกเขากลับมายังบ้านเกิดเมืองนอนอีก”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

บาปของอิสราเอล

12เอฟราอิมล้อมกรอบเราด้วยคำโกหก

พงศ์พันธุ์อิสราเอลห้อมล้อมเราด้วยการหลอกลวง

และยูดาห์ดื้อด้านแม้แต่กับพระเจ้า

ซึ่งเป็นองค์บริสุทธิ์ผู้ซื่อสัตย์