ሆሴዕ 1 – NASV & BDS

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 1:1-11

1በይሁዳ ነገሥታት በዖዝያን፣ በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን እንዲሁም በእስራኤል ንጉሥ በዮአስ1፥1 በዕብራይስጥ ዮአስ የሚለው ቃል የኢዮአስ አማራጭ ትርጕም ነው ልጅ በኢዮርብዓም ዘመን ወደ ብኤሪ ልጅ ወደ ሆሴዕ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

የሆሴዕ ሚስትና ልጆቹ

2እግዚአብሔር በሆሴዕ መናገር በጀመረ ጊዜ፣ እግዚአብሔር “ምድሪቱ ከእግዚአብሔር ተለይታ ታላቅ ምንዝርና እያደረገች ስለሆነ፣ ሄደህ አመንዝራ ሴት አግባ፤ የምንዝርና ልጆችንም ለራስህ ውሰድ” አለው። 3ስለዚህ እርሱ የዴቤላይምን ሴት ልጅ ጎሜርን አገባ፤ እርሷም ፀነሰች፤ ወንድ ልጅም ወለደችለት።

4እግዚአብሔርም ሆሴዕን እንዲህ አለው፤ “በኢይዝራኤል ስለ ተፈጸመው ግድያ የኢዩን ቤት በቅርቡ ስለምቀጣና የእስራኤልንም መንግሥት እንዲያከትም ስለማደርግ፣ ስሙን ኢይዝራኤል ብለህ ጥራው። 5በዚያም ቀን በኢይዝራኤል ሸለቆ፣ የእስራኤልን ቀስት እሰብራለሁ።”

6ጎሜር እንደ ገና ፀነሰች፤ ሴት ልጅም ወለደች፤ እግዚአብሔርም ሆሴዕን እንዲህ አለው፤ “ይቅር እላቸው ዘንድ ለእስራኤል ቤት ከእንግዲህ ስለማልራራላቸው፣ ስሟን ሎሩሃማ1፥6 ሎሩሃማ ማለት ያልተወደደች ማለት ነው ብለህ ጥራት። 7ነገር ግን ለይሁዳ ቤት እራራለሁ፤ በቀስት ወይም በሰይፍ ወይም በጦርነት ወይም በፈረሶችና በፈረሰኞች ሳይሆን በአምላካቸው በእግዚአብሔር አድናቸዋለሁ።”

8ጎሜር፣ ሎሩሃማን ጡት ካስጣለች በኋላ ሌላ ወንድ ልጅ ወለደች። 9እግዚአብሔርም እንዲህ አለው፤ “ሎዓሚ1፥9 ሎዓሚ ማለት ሕዝቤ አይደለም ማለት ነው ብለህ ጥራው፤ ምክንያቱም እናንተ ሕዝቤ አይደላችሁም፤ እኔም አምላካችሁ አይደለሁምና።

10“ይሁን እንጂ እስራኤላውያን ሊሰፈርና ሊቈጠር እንደማይችል እንደ ባሕር አሸዋ ይሆናሉ፤ ‘ሕዝቤ አይደላችሁም’ በተባሉበት ቦታ፣ ‘የሕያው አምላክ ልጆች’ ተብለው ይጠራሉ። 11የይሁዳ ሕዝብና የእስራኤል ሕዝብ እንደ ገና አንድ ይሆናሉ፤ አንድ መሪም ይሾማሉ፤ አንድ ሆነውም በምድሪቱ ይገንናሉ፤ የኢይዝራኤል ቀን ታላቅ ይሆናልና።

La Bible du Semeur

Osée 1:1-9

Les actes symboliques

1L’Eternel adressa la parole à Osée, fils de Beéri, sous les règnes d’Ozias, de Yotam, d’Ahaz et d’Ezéchias, rois de Juda, et sous le règne de Jéroboam, fils de Joas, roi d’Israël1.1 Sur cette période, voir 2 R 15 à 20 ; 2 Ch 27 à 32. roi d’Israël: Jéroboam (793 à 753 av. J.-C.). rois de Juda, en tenant compte des co-régences : Ozias (792 à 740 av. J.-C.), Yotam (750 à 732 av. J.-C.), Ahaz (735 à 715 av. J.-C.) et Ezéchias (727 à 698 ou 686 av. J.-C.)..

Le mariage de Dieu avec Israël

2Première partie des paroles que l’Eternel prononça par Osée :

L’Eternel dit à Osée : Va, prends une femme qui se livre à la prostitution, et des enfants nés de la prostitution, car le pays se vautre dans la prostitution en se détournant de l’Eternel1.2 Le culte de Baal et d’Astarté, avec leurs rites de fécondité, s’accompagnait de la prostitution sacrée (voir v. 10 et note)..

3Alors Osée alla prendre Gomer, de Diblaïm. Elle devint enceinte et lui donna un fils. 4L’Eternel lui dit : Appelle-le Jizréel, car d’ici peu de temps, je ferai rendre compte à la dynastie de Jéhu des meurtres commis à Jizréel1.4 Voir 2.2 et note ; 2 R 9 et 10. et je mettrai fin à la royauté d’Israël. 5En ce jour-là, je briserai l’arc d’Israël dans la vallée de Jizréel.

6Gomer fut de nouveau enceinte et mit au monde une fille. L’Eternel dit à Osée : Appelle-la Lo-Rouhama (la Non-Aimée), car, à l’avenir, je ne manifesterai plus d’amour à la communauté d’Israël, et je ne lui accorderai plus mon pardon.

7Cependant, je manifesterai de l’amour à la communauté de Juda, et moi, l’Eternel son Dieu, je la sauverai. Je la sauverai moi-même – et non pas par l’arc, par l’épée ou la guerre, par les chevaux et les équipages de chars.

8Après avoir sevré Lo-Rouhama, Gomer fut encore enceinte et elle donna naissance à un fils.

9L’Eternel dit à Osée : Appelle-le Lo-Ammi (Pas mon peuple) car vous n’êtes pas mon peuple, et moi, Je suis, je ne suis rien pour vous1.9 Reprise du verbe d’Ex 3.14 où Dieu révèle son nom : Je suis..