아가 3 – KLB & NASV

Korean Living Bible

아가 3:1-11

1(여자) 내가 잠자리에서 밤새도록 사랑하는 님을 그리워하고 찾아도 찾지 못 하였네.

2내가 일어나 거리와 광장으로 나가서 사랑하는 님을 찾았으나 만나지 못하였다.

3야경꾼들을 만나 내 사랑하는 님을 보았느냐고 물었지.

4그들을 떠난 즉시 나는 내 사랑하는 님을 만났네. 그래서 그를 붙잡아 가지 못하게 하고 내가 태어난 우리 집 방으로 데리고 갔다.

5예루살렘 여자들아, 내가 너희에게 3:5 원문에는 ‘노루와 들사슴으로’간절히 부탁한다. 제발 우리의 사랑을 방해하지 말아다오.

세 번째 노래

6(여자) 상인들의 향품으로 만든 몰약과 유향의 향기를 날리며 연기 기둥처럼 사막에서 오는 자가 누구인가?

7보라, 이스라엘의 용감한 병사 60명의 호위를 받으며 솔로몬의 마차가 오고 있다.

8그 경호병들은 칼을 잘 쓰는 역전의 용사들이며 밤에도 왕을 경호하려고 모두 허리에 칼을 찼구나.

9솔로몬왕이 레바논의 나무로 자기 마차를 만들었으니

10그 기둥은 은이요 바닥은 금이며 앉는 자리는 자색 천으로 만들었고 그 내부는 예루살렘 여자들의 사랑으로 꾸며졌네.

11시온의 여자들아, 나와서 솔로몬왕을 보아라. 결혼식 날 그의 마음이 기쁠 때 그 어머니가 씌워 준 면류관을 보아라.

New Amharic Standard Version

ማሕልየ መሓልይ 3:1-11

1ሌሊቱን ሙሉ በዐልጋዬ ላይ ሆኜ፣

ውዴን ተመኘሁ፤

ተመኘሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

2ተነሥቼ ወደ ከተማዪቱ እወጣለሁ፤

በዋና ዋና መንገዶችና በአደባባዮች እዘዋወራለሁ፤

ውዴንም እፈልገዋለሁ፤

ስለዚህም ፈለግሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

3በከተማዪቱ ውስጥ ሲዘዋወሩ፣

የከተማዪቱ ጠባቂዎች አገኙኝ፤

እኔም፣ “ውዴን አይታችኋል?”

አልኋቸው።

4ከእነርሱ ጥቂት ዕልፍ እንዳልሁ፣

ውዴን አገኘሁት፤ ያዝሁት፤

ወደ እናቴ ቤት እስካመጣው፣

በማሕፀን ወደ ተሸከመችኝም ዕልፍኝ

እስካገባው ድረስ አልለቀውም።

5እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፤

ራሱ እስኪፈልግ ድረስ፣

ፍቅርን እንዳታስነሡት ወይም እንዳትቀሰቅሱት፣

በሚዳቋና በሜዳ ዋሊያ አማጥናችኋለሁ።

6ከከርቤና ከዕጣን፣

ከነጋዴም ቅመማ ቅመም ሁሉ በተዘጋጀ ሽቱ፣

መዐዛዋ የሚያውድ፣

እንደ ጢስ ዐምድ ከምድረ በዳ የምትወጣው ይህች ማን ናት?

7እነሆ፤ የሰሎሞን ሠረገላ

በታዋቂዎቹ የእስራኤል መኳንንት፣

ስድሳ ጦረኞች ታጅባለች፤

8ሁሉም ሰይፍ የታጠቁ፣

ሁሉም በጦርነት የተፈተኑ ናቸው፤

የሌሊት አደጋን ለመከላከልም፣

እያንዳንዳቸው ሰይፋቸውን በወገባቸው ታጥቀዋል።

9ንጉሥ ሰሎሞን የራሱን ሠረገላ ሠራ፤

የሠራውም ከሊባኖስ በመጣ ዕንጨት ነው።

10ምሰሶዎቹን ከብር፣

መደገፊያውንም ከወርቅ ሠራ፤

መቀመጫውም በሐምራዊ ሐር የተሸፈነ ነው፤

ውስጡም በኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፣

አምሮ የተለበጠ ነው።3፥10 ወይም የተለበጠውም ውስጥ፣ ከኢየሩሳሌም ቈነጃጅት የሆነ የፍቅር ስጦታ

11እናንት የጽዮን ቈነጃጅት ውጡ፤

ንጉሥ ሰሎሞን አክሊሉን ደፍቶ እዩት፤

ዘውዱም ልቡ ሐሤት ባደረገባት፣

በዚያች በሰርጉ ዕለት፣

እናቱ የደፋችለት ነው።