돌에 기록된 율법
1그러고서 모세는 이스라엘 지도자들과 함께 백성들에게 이렇게 명령 하였다. “여러분은 내가 오늘 여러분에게 명령하는 모든 것을 지켜야 합니다.
2-4여러분이 요단강을 건너 여러분의 하나 님 여호와께서 주시는 기름지고 비옥한 땅에 들어갈 때 에발산에 큰 돌들을 세우고 석회를 칠한 다음 이 모든 법과 규정을 거기에 기록하십시오.
5-6그리고 여러분은 거기서 여러분의 하나 님 여호와를 위해 철 연장을 사용하지 말고 다듬지 않은 자연석으로 제단을 쌓고 여러분의 하나님 여호와께 불로 태워 바치는 번제를 드려야 합니다.
7또 여러분은 거기서 화목제를 드리고 여러분의 하나님 여호와 앞에서 먹고 즐거워하십시오.
8여러분은 그 돌들 위에 이 율법의 모든 말씀을 분명하게 기록해 두어야 합니다.”
9그런 다음 모세는 레위 제사장들과 함께 이스라엘 백성에게 이렇게 말하였다. “이스라엘 백성 여러분, 귀를 기울이고 잘 들으십시오. 여러분은 오늘 여러분의 하나님 여호와의 백성이 되었습니다.
10그러므로 여러분의 하나님 여호와께 순종하고 오늘 내가 여러분에게 가르친 명령과 규정을 지켜야 합니다.”
에발산에서 선포하는 저주
11바로 그 날 모세는 백성들에게 이렇게 명령하였다.
12“여러분이 요단강을 건너가면 시므온 지파, 레위 지파, 유다 지파, 잇사갈 지파, 요셉 지파, 베냐민 지파는 축복을 선포하기 위해 그리심산에 서고
13르우벤 지파, 갓 지파, 아셀 지파, 스불론 지파, 단 지파, 납달리 지파는 저주를 선포하기 위해 에발산에 서십시오.
14그리고 레위 사람들이 큰 소리로 백성에게 다음과 같이 외치면 백성들은 ‘아멘’ 하고 대답하십시오.
በጌባል ተራራ ላይ የቆመ መሠዊያ
1ሙሴና የእስራኤል አለቆች ሕዝቡን እንዲህ ብለው አዘዙ፤ “ዛሬ የማዝዛችሁን እነዚህን ትእዛዞች ሁሉ ጠብቁ፤ 2አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ወደሚሰጥህ ምድር ለመግባት ዮርዳኖስን በተሻገራችሁ ጊዜ፣ ጥቂት ትልልቅ ድንጋዮችን አቁምና በኖራ ቅባቸው። 3የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሰጠህ ተስፋ መሠረት፣ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ወደሚሰጥህ ምድር ለመግባት ዮርዳኖስን ስትሻገር፣ የዚህን ሕግ ቃላት ሁሉ ጻፍባቸው። 4ዮርዳኖስን እንደ ተሻገርህም፣ ዛሬ ባዘዝሁህ መሠረት እነዚህን ድንጋዮች በጌባል ተራራ ላይ ትከላቸው፤ በኖራም ቅባቸው። 5እዚያም ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የድንጋይ መሠዊያ ሥራ፤ በድንጋዮቹም ላይ ማናቸውንም የብረት መሣሪያ አታሳርፍባቸው። 6የአምላክህን የእግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) መሠዊያ ካልተጠረበ ድንጋይ ሥራ፤ በላዩም ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሚቃጠል መሥዋዕት አቅርብበት። 7በዚያም የኅብረት መሥዋዕት27፥7 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት በመባል ይታወቃል ሠዋ፤ ብላም፤ በአምላክህ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ደስ ይበልህ። 8በድንጋዮቹ ላይ የዚህን ሕግ ቃላት ሁሉ ግልጽ አድርገህ ጻፍባቸው።”
በጌባል ተራራ ላይ የተነገረ መርገም
9ሙሴና ሌዋውያን ካህናትም ለእስራኤል ሁሉ እንዲህ አሉ፤ “እስራኤል ሆይ፤ ጸጥ ብለህ አድምጥ! አንተ ዛሬ የአምላክህ የእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ሕዝብ ሆነሃል፤ 10አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ታዘዝ፤ ዛሬ የምሰጥህን ትእዛዙንና ሥርዐቱን ጠብቅ።”
11ሙሴ በዚያኑ ዕለት ሕዝቡን እንዲህ ብሎ አዘዘ፦
12ዮርዳኖስን በተሻገራችሁ ጊዜ፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ይሳኮር፣ ዮሴፍና ብንያም ሕዝቡን ለመባረክ በገሪዛን ተራራ ላይ ይቁሙ። 13ሮቤል፣ ጋድ፣ አሴር፣ ዛብሎን፣ ዳንና ንፍታሌምም በጌባል ተራራ ላይ ለመርገም ይቁሙ።
14ሌዋውያን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ለእስራኤል ሕዝብ ሁሉ እንዲህ ብለው ይናገሩ፦
15“የእጅ ጥበብ ባለሙያ የሠራውን፣ በእግዘአብሔር (ያህዌ) ዘንድ አስጸያፊ የሆነውን ምስል የሚቀርጽ ወይም ጣዖትን የሚያበጅ፣ በስውርም የሚያቆም ሰው የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
16“አባቱን ወይም እናቱን የሚያቃልል የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን! ይበል።
17“የባልንጀራውን የድንበር ድንጋይ ከቦታው የሚያንቀሳቅስ የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
18“ዐይነ ስውሩን በተሳሳተ መንገድ የሚመራ፣ የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
19“በመጻተኛው፣ አባት በሌለውና በመበለቲቱ ላይ ፍትሕ የሚያዛባ የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
20“ከአባቱ ሚስት ጋር የሚተኛ የተረገመ ይሁን፤ የአባቱን መኝታ ያረክሳልና።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
21“ከማናቸውም እንስሳ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚያደርግ የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
22“የአባቱ ወይም የእናቱ ልጅ ከሆነችው እኅቱ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚፈጽም የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
23“ከዐማቱ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚፈጽም የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
24“በድብቅ ባልንጀራውን የሚገድል የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
25“ንጹሕን ሰው ለመግደል ጕቦ የሚቀበል የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።
26“የዚህን ሕግ ቃሎች በመፈጸም የማይጸና የተረገመ ይሁን።”
ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።