민수기 2 – KLB & NASV

Korean Living Bible

민수기 2:1-34

각 지파의 진지 배치

1여호와께서 또 모세와 아론에게 말씀하셨다. “이스라엘 백성은 성막 주위에 각

2지파별로 기를 중심하여 진을 쳐라.

3-4성막 동쪽에 진을 칠 세 지파는 암미나 답의 아들 나손이 이끄는 74,600명의 병력을 가진 유다 지파,

5-6그 옆에는 수알의 아들 느다넬이 이끄 는 54,400명의 병력을 가진 잇사갈 지파,

7-8그 옆에는 헬론의 아들 엘리압이 이끄는 57,400명의 병력을 가진 스불론 지파이다.

9이와 같이 유다 진영에 진을 칠 전체 병력은 186,400명이다. 이들이 선두에서 행군하게 하라.

10-11“성막 남쪽에 진을 칠 세 지파는 스데울 의 아들 엘리술이 이끄는 46,500명의 병력을 가진 르우벤 지파,

12-13그 옆에는 수리삿대의 아들 슬루미엘 이 이끄는 59,300명의 병력을 가진 시므온 지파,

14-15그 옆에는 2:14-15 또는 ‘드우엘’르우엘의 아들 엘리아삽이 이끄는 45,650명의 병력을 가진 갓 지파이다.

16이와 같이 르우벤 진영에 진을 칠 전체 병력은 151,450명이다. 이들이 두 번째로 행군하게 하라.

17“그 다음에는 레위 지파가 성막을 가지고 행렬 중앙에서 행군하게 하라. 그리고 행군할 때에는 진을 치는 순서대로 각 지파가 기를 앞세우고 자기 위치에서 행군해야 한다.

18-19“성막 서쪽에 진을 칠 세 지파는 암미훗 의 아들 엘리사마가 이끄는 40,500명의 병력을 가진 에브라임 지파,

20-21그 옆에는 브다술의 아들 가말리엘이 이끄는 32,200명의 병력을 가진 므낫세 지파,

22-23그 옆에는 기드오니의 아들 아비단이 이끄는 35,400명의 병력을 가진 베냐민 지파이다.

24이와 같이 에브라임 진영에 진을 칠 전체 병력은 108,100명이다. 이들이 세 번째로 행군하게 하라.

25-26“그리고 성막 북쪽에 진을 칠 세 지파 는 암미삿대의 아들 아히에셀이 이끄는 62,700명의 병력을 가진 단 지파,

27-28그 옆에는 오그란의 아들 바기엘이 이 끄는 41,500명의 병력을 가진 아셀 지파,

29-30그 옆에는 에난의 아들 아히라가 이끄 는 53,400명의 병력을 가진 납달리 지파이다.

31이와 같이 단 진영에 진을 칠 전체 병력은 157,600명이다. 이들이 제일 뒤에서 행군하게 하라.”

32이상과 같이 이스라엘 백성 가운데 징집 명단에 등록된 전체 인원은 603,550명이었다.

33그러나 여기에는 여호와께서 모세에게 명령하신 대로 레위인은 포함되지 않았다.

34이스라엘 백성은 여호와께서 모세에게 명령하신 대로 각 지파별로 기를 앞세우고 진을 치기도 하고 행군하기도 하였다.

New Amharic Standard Version

ዘኍል 2:1-34

የየነገዱ አሰፋፈር

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤ 2“እስራኤላውያን ከምስክሩ ድንኳን ትይዩ ዙሪያውን ጥቂት ራቅ ብለው እያንዳንዱ ሰው በየዐርማውና በየቤተ ሰቡ ምልክት ሥር ይስፈር።”

3በምሥራቅ በኩል በፀሓይ መውጫ፤

የይሁዳ ምድብ፤ በየሰራዊቱና በዐርማቸው ሥር ይስፈር፤ የይሁዳ ሕዝብ አለቃ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን ነው፤ 4የሰራዊቱም ብዛት ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነው።

5ከእነዚህ ቀጥሎ የይሳኮር ነገድ ይሰፍራል፤ የይሳኮር ሕዝብ አለቃ የሶገር ልጅ ናትናኤል ሲሆን፣ 6የሰራዊቱም ብዛት አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነው።

7ከዚያም የዛብሎን ነገድ ይቀጥላል፤ የዛብሎን ሕዝብ አለቃ የኬሎን ልጅ ኤልያብ ሲሆን፣ 8የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነው።

9በየሰራዊታቸው ሆነው ከአይሁድ ምድብ የተመዘገቡ አንድ መቶ ሰማንያ ስድስት ሺሕ አራት መቶ ናቸው፤ እነዚህ አስቀድመው ይወጣሉ።

10በደቡብ በኩል፤

የሮቤል ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የሮቤል ሕዝብ አለቃ የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር ሲሆን፣ 11የሰራዊቱም ብዛት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነው።

12ከእነዚህ ቀጥሎ የስምዖን ነገድ ይሰፍራል፤ የስምዖን ሕዝብ አለቃ የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል ሲሆን፣ 13የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነው።

14ከዚያም የጋድ ነገድ ይቀጥላል፤ የጋድ ሕዝብ አለቃ የራጉኤል2፥14 ብዙ የማሶሬቲክ፣ የኦሪት ሳምራውያንና የቩልጌት ቅጆች ጸዑኤል ይላሉ (ዘኍ 1፥14 ይመ)፤ አያሌ የማሶሬቲክ ቅጆች ግን ከዚህ ይስማማሉ። ልጅ ኤሊሳፍ ሲሆን፣ 15የሰራዊቱም ብዛት አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነው።

16በየሰራዊታቸው ሆነው ከሮቤል ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ አምሳ አንድ ሺሕ አራት መቶ አምሳ ናቸው፤ እነዚህ ቀጥለው ይመጣሉ።

17ከዚህ በኋላ የመገናኛው ድንኳንና የሌዋውያን ምድብ በመካከል ሆነው ይጓዛሉ፤ እያንዳንዳቸውም አሰፋፈራቸውን በመከተል ቦታቸውን ጠብቀው በዐርማቸው ሥር ይጓዛሉ።

18በምዕራብ በኩል፤

የኤፍሬም ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የኤፍሬም ሕዝብ አለቃ የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ ሲሆን፣ 19የሰራዊቱም ብዛት አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

20ከእነዚህም የምናሴ ነገድ ይቀጥላል፣ የምናሴ ሕዝብ አለቃ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል ሲሆን፣ 21የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነው።

22ከዚያም የብንያም ነገድ ይቀጥላል፣ የብንያም ሕዝብ አለቃ የጋዴዮን ልጅ አቢዳን ሲሆን፣ 23የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

24በየሰራዊታቸው ሆነው ከኤፍሬም ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ ስምንት ሺሕ አንድ መቶ ናቸው፤ እነዚህ ሦስተኛ ሆነው ይመጣሉ።

25በሰሜን በኩል፤

የዳን ምድብ ሰራዊት በዐርማው ሥር ይሆናል፤ የዳን ሕዝብ አለቃ የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር ሲሆን፣ 26የሰራዊቱም ብዛት ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነው።

27የአሴር ነገድ ከእነዚህ ቀጥሎ ይሰፍራል፤ የአሴር ሕዝብ አለቃ የኤክራን ልጅ ፋግኤል ሲሆን፣ 28የሰራዊቱም ብዛት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

29ከዚያም የንፍታሌም ነገድ ይቀጥላል፤ የንፍታሌም ሕዝብ አለቃ የዔናን ልጅ አኪሬ ሲሆን፣ 30የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

31በየሰራዊታቸው ሆነው ከዳን ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች ሁሉ አንድ መቶ አምሳ ሰባት ሺሕ ስድስት መቶ ናቸው፤ እነርሱም በዐርማቸው ሥር በመጨረሻ ይመጣሉ።

32በየቤተ ሰባቸው፣ በየምድባቸውና በየሰራዊታቸው የተመዘገቡት እስራኤላውያን ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ናቸው፤ 33ያም ሆኖ ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ሌዋውያኑ ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር አልተቈጠሩም።

34ስለዚህ እስራኤላውያን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ያዘዘውን ሁሉ አደረጉ፤ በየዐርማውም ሥር የሰፈሩትና፣ እያንዳንዳቸው በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የተጓዙት በዚህ ሁኔታ ነበር።