詩篇 94 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

詩篇 94:1-23

94

1-2復讐の神である主よ。

あなたのご栄光を輝かせてください。

地上の人々をさばき、

おごり高ぶる者どもを罰してください。

3主よ、いつまで悪者は勝ち誇り、

有頂天でいるのですか。

4あの横柄なことば、尊大な態度、

自慢げな様子をごらんください。

5ああ主よ。彼らは、あなたが愛しておられる人々を

あれほどまで悩ませています。

6-7「主に知れるわけがない。

神は気にかけることもない」と、

未亡人や移民、みなしごなどを殺します。

8愚か者どもよ。

9耳と目をお造りになった神が、

耳が聞こえず、目が見えないということがあろうか。

10世界をおさばきになる方が、

どうしておまえたちの罪を見過ごしになさるだろうか。

いっさいのことをお見通しの神に、

おまえたちの悪事がばれないはずはないのだ。

11主は、人の考えや判断にはどれほど限りがあり、

無益であるかを、よくご存じです。

12-13ですから、痛い目に会わせることによって、

私たちを神の道へと導かれるのです。

一方、神は敵に罠をしかけて滅ぼし、

私たちに、ひと時の休息を与えてくださいます。

14主は決して、ご自分の民を見捨てたりなさいません。

宝のように思っておられるのですから。

15裁判は再び公平さを取り戻し、

正直な人が喜ぶようになります。

16だれが、盾となって

私を悪者から守ってくれるのでしょう。

17もし主の助けの手が差し伸べられなかったら、

今ごろ私は死んでいたことでしょう。

18「神よ、私はよろめいています」と

叫んだ時、主は救い上げてくださいました。

19神よ、何もかもが信じられず動揺してしまうとき、

私の心を静め、新しい希望を与え、

快活さを取り戻させてください。

20どうか、悪が正義を打ち負かす腐敗した政治を、

あなたが支持し、

存続させることがありませんように。

21-22罪もない人を死刑にする者を、

見過ごされることがありませんように。

主は私のとりで、

難を避けるための、揺るぎない岩です。

23主は悪者どもの罪が、

自らの頭上に返るようにしてくださいました。

そして悪者の計略を逆用し、

彼らを滅ぼしてくださいます。

New Amharic Standard Version

መዝሙር 94:1-23

መዝሙር 94

የእግዚአብሔር ፍትሕ

1የበቀል አምላክ፣ አንተ እግዚአብሔር ሆይ፤

የበቀል አምላክ ሆይ፤ ደምቀህ ተገለጥ።

2አንተ የምድር ዳኛ ሆይ፤ ተነሥ፤

ለትዕቢተኞች የእጃቸውን ስጣቸው።

3ክፉዎች እስከ መቼ እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፉዎች እስከ መቼ ይፈነጫሉ?

4የእብሪት ቃላት ያዥጐደጕዳሉ፤

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ጕራ ይነዛሉ።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብህን አደቀቁ፤

ርስትህንም አስጨነቁ።

6መበለቲቱንና መጻተኛውን ገደሉ፤

የድኻ ዐደጉንም ነፍስ አጠፉ።

7እነርሱም “እግዚአብሔር አያይም፤

የያዕቆብም አምላክ አያስተውልም” አሉ።

8እናንት በሕዝቡ መካከል ያላችሁ ደነዞች፤ ልብ በሉ፤

እናንት ቂሎች፤ ጥበበኞች የምትሆኑት መቼ ነው?

9ጆሮን የተከለው እርሱ አይሰማምን? ዐይንንስ የሠራ እርሱ አያይምን?

10ሕዝቦችን በተግሣጽ ወደ መንገድ የሚመልስ፣

ዕውቀትንስ ለሰው ልጆች የሚያስተምር አይቀጣምን?

11እግዚአብሔር የሰው ሐሳብ መና፣

ከንቱም እንደ ሆነ ያውቃል።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ የምትገሥጸው፣

ከሕግህም የምታስተምረው ሰው ምስጉን ነው።

13ለኀጢአተኞች ጕድጓድ እስኪማስላቸው ድረስ፣

እርሱን ከመከራ ታሳርፈዋለህ።

14እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥልምና፤

ርስቱንም አይተውም።

15ፍርድ ተመልሶ በጽድቅ አሠራር ላይ ይመሠረታል፤

ልባቸውም ቀና የሆነ ሁሉ ይከተሉታል።

16ክፉዎችን የሚቋቋምልኝ ማን ነው?

ከክፉ አድራጊዎችስ ጋር የሚሟገትልኝ ማን ነው?

17እግዚአብሔር ረዳቴ ባይሆን ኖሮ፣

ነፍሴ ወደ ዝምታው ዓለም ፈጥና በወረደች ነበር።

18እኔ፣ “እግሬ አዳለጠኝ” ባልሁ ጊዜ፣

እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ደግፎ ያዘኝ።

19የውስጤ ጭንቀት በበዛ መጠን፣

ማጽናናትህ ነፍሴን ደስ አሰኛት።

20ዐመፃን ሕጋዊ የሚያደርግ፣

የጥፋት ዙፋን ከአንተ ጋር ሊያብር ይችላልን?

21በጻድቁ ላይ ተሰልፈው ይወጣሉ፤

በንጹሑም ላይ ሞት ይፈርዳሉ።

22ለእኔ ግን እግዚአብሔር ምሽግ፣

አምላኬም መጠጊያ ዐለት ሆኖኛል።

23በደላቸውን ወደ ራሳቸው ይመልሳል፤

በክፋታቸውም ያጠፋቸዋል፤

እግዚአብሔር አምላካችን ይደመስሳቸዋል።