箴言 知恵の泉 4 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 4:1-27

4

犠牲を払ってでも知恵を得なさい

1-2さあ、父親の話を聞くように、

私の言うことを聞きなさい。

知恵のある人になるために、

私が教える真理を勉強しなさい。

顔をそむけてはいけません。

3私も若いころは、

母にはひとり息子としてかわいがられ、

父とはよく、いろいろなことを話し合ったものです。

4そんな時、父は口ぐせのように、

こう言い聞かせてくれました。

「よく聞きなさい。

私のことばと教えを大切にすれば、

一生幸せに暮らせる。

5何よりも、知恵と悟りのある人間になりなさい。

このことを決して忘れてはならない。」

6知恵があなたを守ってくれます。

しっかり心に留め、大切にしなさい。

7知恵のある人になるには、

まず賢くなろうと決心することです。

それが、物事を正しく判断する力と

知恵を養うのです。

8-9知恵を高めれば、

あなたも高められます。

知恵を抱きしめると、

それはあなたに大きな誉れを与えます。

10わが子よ。私の言うようにしなさい。

そうすれば長生きし、生涯幸せに過ごせます。

11正しい生活をするのが、いちばん賢い生き方です。

この大切な真理を学びなさい。

12そのように生きれば、もたつかないで歩み、

走ってもつまずきません。

13私の訓戒を実行し、

忘れないようにしなさい。

それはあなたにいのちとなるからです。

14悪者のまねをしてはいけません。

15彼らの集まる場所に近寄らず、

そこを避けて通りなさい。

16彼らは一日分の悪事を働かないと、

その夜はおちおち眠ることもできず、

人をつまずかせないうちは

ゆっくり休むこともできません。

17悪いことをし、暴力をふるわないと

生きていられないのです。

18神は正しい人の道を優しく見守り、

真昼のように明るく照らしてくださいます。

19一方悪者は、暗がりでうろうろ手探りし、

あちこちでつまずくのです。

20わが子よ。私のことばをよく聞きなさい。

21それを肝に銘じ、忘れないようにしなさい。

22そうすることがあなたのいのちとなり、

健やかにするのです。

23何よりも、あなたの心を守りなさい。

心は生活全体に影響を与えるからです。

24悪い女の慎みのない口づけをはねのけなさい。

悪い女に近づいてはいけません。

25ただまっすぐ前を見つめ、

うしろを振り返らないことです。

26足もとに気をつけ、

確実に進みなさい。

27横道にそれてはいけません。

危険だとわかったら、一目散に引き返しなさい。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 4:1-27

ጥበብ ከሁሉ በላይ መሆኗ

1ልጆቼ ሆይ፤ የአባትን ምክር አድምጡ፤

ልብ ብላችሁ ስሙ፤ ማስተዋልንም ገንዘብ አድርጉ።

2በጎ ትምህርት እሰጣችኋለሁ፤

ስለዚህ ትምህርቴን አትተዉ።

3በአባቴ ቤት ገና ለግላጋ ወጣት፣

ለእናቴም አንድ ልጇ ብቻ በነበርሁ ጊዜ፣

4አባቴ እንዲህ ሲል አስተማረኝ፤

“ቃሌን በሙሉ በልብህ ያዝ፤

ትእዛዜንም ጠብቅ፤ በሕይወት ትኖራለህ።

5ጥበብን አግኛት፤ ማስተዋልን ያዛት፤

ቃሌን አትርሳ፤ ከእርሷም ዘወር አትበል።

6ጥበብን አትተዋት፤ እርሷም ከለላ ትሆንሃለች፤

አፍቅራት፤ እርሷም ትጠብቅሃለች።

7ጥበብ ታላቅ ነገር ናት፤ ስለዚህ ጥበብን አግኛት፤

ያለህን ሁሉ4፥7 ወይም ያገኘኸውን ሁሉ ብታስከፍልህም ማስተዋልን ገንዘብህ አድርጋት።

8ክብርን ስጣት፤ ከፍ ከፍ ታደርግሃለች፤

ዕቀፋት፤ ታከብርሃለች፤

9በራስህ ላይ ሞገሳማ አክሊል ትደፋልሃለች፤”

የክብር ዘውድም ታበረክትልሃለች።

10ልጄ ሆይ፤ አድምጠኝ፤ ቃሌንም ልብ በል፤

የሕይወት ዘመንህም ትበዛለች።

11በጥበብ ጐዳና አስተምርሃለሁ፤

ቀጥተኛውንም መንገድ አሳይሃለሁ።

12ስትሄድ ርምጃህ አይሰናከልም፤

ስትሮጥም አትደናቀፍም።

13ምክርን አጥብቀህ ያዛት፤ አትልቀቃት፤

ጠብቃት፤ ሕይወትህ ናትና።

14ወደ ኀጥኣን ጐዳና እግርህን አታንሣ፤

በክፉ ሰዎች መንገድ አትሂድ፤

15ከዚያ አትድረስ፤ አትጓዝበት፤

ሽሸው፤ መንገድህን ይዘህ ሂድ፤

16ክፉ ካላደረጉ አይተኙምና፤

ሰውን ካላሰናከሉ እንቅልፍ በዐይናቸው አይዞርም።

17የክፋት እንጀራ ይበላሉ፤

የዐመፅ ወይን ጠጅ ይጠጣሉ።

18የጻድቃን መንገድ ሙሉ ቀን እስኪሆን ድረስ፣

ብርሃኑ እየጐላ እንደሚሄድ የማለዳ ውጋጋን ነው።

19የክፉዎች መንገድ ግን እንደ ድቅድቅ ጨለማ ነው፤

ምን እንደሚያሰናክላቸውም አያውቁም።

20ልጄ ሆይ፤ የምነግርህን አስተውል፤

ቃሌንም በጥንቃቄ አድምጥ።

21ከእይታህ አታርቀው፤

በልብህም ጠብቀው፤

22ለሚያገኘው ሕይወት፤

ለመላው የሰው አካልም ጤንነት ነውና።

23ከሁሉም በላይ ልብህን ጠብቅ፤

የሕይወት ምንጭ ነውና።

24ጥመትን ከአፍህ አስወግድ፤

ብልሹ ንግግርም ከከንፈሮችህ ይራቅ።

25ዐይኖችህ በቀጥታ ይመልከቱ፤

ትክ ብለህም ፊት ለፊት እይ።

26የእግርህን ጐዳና አስተካክል፤4፥26 ወይም ተመልከት

የጸናውን መንገድ ብቻ ያዝ።

27ወደ ቀኝ ወደ ግራ አትበል፤

እግርህን ከክፉ ጠብቅ።