箴言 知恵の泉 12 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 12:1-28

12

1人の言うことを聞く気がある人は、

知識を得ることができます。

叱責に耳をふさぐ者は愚か者です。

2主は正しい人を祝福し、悪人を罰します。

3悪いことをして成功する者はいません。

成功するのは正しい人だけです。

4良い妻は夫の誇り。

悪い妻は夫に肩身のせまい思いをさせ、

事ごとに足を引っ張ります。

5正しい人の考えは正直一筋ですが、

悪人はうそと偽りでこり固まっています。

6悪人は人を責め、神を恐れる人は人をかばいます。

7悪人の家は必ず滅び、

正しい人の家は最後まで存続します。

8見識のある人は、だれからも称賛され、

ひねくれ者はみんなに軽蔑されます。

9高慢で働きもせず、食べるにも事欠くより、

目立たない仕事でもまじめに働き、

食にありつくほうがまさっています。

10正しい人は自分の家畜にまで細かく気を配ります。

しかし神を恐れない人は、

うわべは親切そうでも思いやりがありません。

11こつこつ働けば生活は楽になります。

怠けて遊んでいるのは愚か者だけです。

12曲がった者は仲間の分け前まで欲しがり、

正しい人は自分の物をなげうってでも人を助けます。

13うそをつくとあとで苦しみますが、

正直者にはそんな心配はありません。

14ほんとうのことを言う人も、

こつこつ働く人も必ず報われます。

15愚か者は忠告を無視し、

知恵ある人は人のことばに耳を傾けます。

16愚か者はすぐ怒り、

知恵ある人は侮辱されても冷静です。

17正しい人かどうかは正直さでわかり、

不誠実な人はうそと欺きでわかります。

18批評好きは人を傷つけますが、

知恵ある人のことばは慰め、いやします。

19真実はいつまでも変わらず、

うそで塗り固めたものはすぐにはがれ落ちます。

20悪いことを企む者は、

人をだますことで頭がいっぱいです。

しかし、良いことをする人は、

いつも喜びに満たされています。

21正しい人はどんな災いにも会わず、

悪者には苦しみがつきまといます。

22主は約束を守る人を愛しますが、

約束を破る人はきらいです。

23知恵ある人は知っていても黙っていますが、

愚か者は言いふらして、愚かさをさらけ出します。

24勤勉な人は指導者になり、

怠け者はいつまでたっても成功しません。

25どんなに沈んでいる人も、

励ましのひと言で心が軽くなります。

26正しい人は友の助言を求めますが、

悪者は軽率に突き進んで失敗します。

27無精者は、捕らえた獲物を料理するのも面倒がります。

しかし勤勉な人は、見つけた物は少しもむだにせず、

うまく利用します。

28神を信じる人はいのちの道を歩いているので、

死を恐れることがありません。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 12:1-28

1ተግሣጽን የሚወድድ ዕውቀትን ይወድዳል፤

መታረምን የሚጠላ ግን ደነዝ ነው።

2መልካም ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስ ያገኛል፤

ተንኰለኛውን ግን እግዚአብሔር ይፈርድበታል።

3ሰው በክፋት ላይ ተመሥርቶ ሊጸና አይችልም፤

ጻድቃን ግን ከቦታቸው አይነቃነቁም።

4መልካም ሴት ለባሏ ዘውድ ናት፤

አሳፋሪ ሚስት ግን ዐጥንቱ ውስጥ እንዳለ ንቅዘት ናት።

5የጻድቃን ሐሳብ ቀና ነው፤

የክፉዎች ምክር ግን ሸር አለበት።

6የክፉዎች ቃል ደም ለማፍሰስ ታደባለች፤

የቅኖች ንግግር ግን ይታደጋቸዋል።

7ክፉ ሰዎች ይገለበጣሉ፤ ድራሻቸውም ይጠፋል፤

የጻድቃን ቤት ግን ጸንቶ ይኖራል።

8ሰው በጥበቡ ይመሰገናል፤

ጠማማ ልብ ያላቸው ግን የተናቁ ናቸው።

9የሚበላው ሳይኖረው ከሚኵራራ ይልቅ፣

ራሱን ዝቅ አድርጎ ሠራተኛ የሚያሳድር ይሻላል።

10ጻድቅ ሰው ለእንስሳቱ ይራራል፤

ክፉዎች ራሩ ቢባል እንኳ ዞሮ ዞሮ ሥራቸው ጭካኔ ነው።

11መሬቱን የሚያርስ የተትረፈረፈ ምግብ ያገኛል፤

ከንቱ ተስፋን የሚያሳድድ ግን ማመዛዘን ይጐድለዋል።

12ኀጥኣን የክፉዎችን ምርኮ ይመኛሉ፤

የጻድቅ ሥር ግን ይንሰራፋል።

13ክፉ ሰው በእኩይ ንግግሩ ይጠመዳል፤

ጻድቅ ሰው ግን ከመከራ ያመልጣል።

14ሰው ከከንፈሩ ፍሬ የተነሣ በበጎ ነገር ይሞላል፤

እንደ እጁ ሥራም ተገቢውን ዋጋ ያገኛል።

15ተላላ ሰው መንገዱ ትክክል መስሎ ይታየዋል፤

ጠቢብ ሰው ግን ምክር ይሰማል።

16ተላላ ሰው ቍጣው ወዲያውኑ ይታወቅበታል፤

አስተዋይ ሰው ግን ስድብን ንቆ ይተዋል።

17ሐቀኛ ምስክር በእውነት ይመሰክራል፤

ሐሰተኛ ምስክር ግን ውሸት ይናገራል።

18ግድ የለሽ ቃል እንደ ሰይፍ ይወጋል፤

የጠቢብ አንደበት ግን ፈውስን ያመጣል።

19እውነት የሚናገሩ ከንፈሮች ለዘላለም ጸንተው ይኖራሉ፤

ሐሰተኛ አንደበት ግን ለቅጽበት ያህል ብቻ ነው።

20ክፋትን በሚያውጠነጥኑ ሰዎች ልብ አታላይነት አለ፤

ሰላምን የሚያራምዱ ግን ደስታ አላቸው።

21ጻድቃን ጕዳት አያገኛቸውም፤

ክፉዎች ግን በመከራ የተሞሉ ናቸው።

22እግዚአብሔር ሐሰተኛ ከንፈርን ይጸየፋል፤

በእውነተኞች ሰዎች ግን ደስ ይለዋል።

23አስተዋይ ሰው ዕውቀቱን ይሰውራል፤

የተላሎች ልብ ግን ድንቍርናን ይነዛል።

24ትጉህ እጆች ለገዥነት ሲያበቁ፣

የስንፍና ፍጻሜ ግን የባርነት ሥራ ነው።

25ሥጉ ልብ ሰውን በሐዘን ይወጥራል፤

መልካም ቃል ግን ደስ ያሰኘዋል።

26ጻድቅ ሰው ለወዳጁ መልካም ምክር ይሰጣል፤12፥26 ወይም ለወዳጁ መሪ ሆኖም የዕብራይስጡ ፍች በውል አይታወቅም።

የክፉዎች መንገድ ግን ወደ ስሕተት ይመራቸዋል።

27ሰነፍ ዐድኖ ያመጣውን እንኳ አይጠብስም፤12፥27 ለዚህ ቃል የዕብራይስጡ ትርጓሜ በርግጠኝነት አይታወቅም።

ትጉህ ሰው ግን ለንብረቱ ዋጋ ይሰጣል።

28በጽድቅ መንገድ ላይ ሕይወት አለ፤

በዚያ ጐዳና ላይ ሞት የለም።