ヨブ 記 34 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

ヨブ 記 34:1-37

34

1エリフのことばの続き。

2「賢者の皆さん、私の言うことを聞いていただきたい。

3われわれは、聞きたい音楽を選び、

食べたい料理を選ぶように、

4正しいことには従うという選択をするべきだ。

しかし、まず始めに、

正しいとはどういうことか定義する必要がある。

5ヨブさんがこう言ったからだ。

『私は潔白なのに、神はそうでないと言い、

6私をうそつき呼ばわりする。

私は罪など犯したこともないのに、

恐ろしい罰を受けているのだ。』

7-9ヨブさんのように尊大な人間が、

ほかにいるだろうか。

何しろ、『神を喜ばせることなど時間の無駄だ』

と言うほどだから、

悪者たちとよほど親しくしていたに違いない。

10理解力のある皆さん、私の言うことを聞いてほしい。

神が罪を犯さないことぐらい

子どもだって知っている。

11大切なのはむしろ、神が罪人を罰するということだ。

12神は絶対に悪を行わず、

正義を曲げないということほど

確かなことがあるだろうか。

13ただ神だけが、地上を支配する権威を持ち、

正義をもって全世界を治める。

14神がご自分の御霊を取り去ったら、

15いのちあるものはみな姿を消し、人は元のちりに帰る。

16私のことばに耳を傾け、

これから言うことを理解してほしい。

17もし、神が正義を憎むお方だとしたら、

この世を治めることなどできるだろうか。

あなたは、全能の裁判官をとがめるつもりか。

18王や高貴な人に向かって、

『おまえたちは不正を働く悪人だ』と言うこの神を、

とがめるつもりか。

19神は、どんなに身分の高い者をも

特別に重んじることなく、

貧しい人より金持ちを

多少でもえこひいきしたりしない。

どんな人間も、神が造ったからだ。

20彼らはあっという間に死ぬ。

身分の高い者も低い者も、真夜中に突然、

人の手によらないで取り去られる。

21神はすべての人の行動に目を注ぎ、

何もかも見通している。

22悪人が神の視線から身を隠せるような暗闇はない。

23だから、人を神の法廷に引き立てるには、

何か大きな罪を犯すのを待つまでもない。

24神は最高権力者を

取り調べることもなく失脚させ、

他の人を代わりに立てる。

25彼らのすることを監視し、

一夜のうちにそれをくつがえし、彼らを滅ぼす。

26また、公衆の面前で、

彼らを悪者として打ちたたく。

27彼らが神から離れてわき道にそれ、

28貧しい者の叫びが神の耳に届いたからだ。

神は虐待される者の叫びを聞く。

29-30神が沈黙を守っているからといって、

だれが神を非難できよう。

神は、悪者が支配権をにぎらないようにして、

国を滅亡から救う。

その一方で、いとも簡単に一つの国を葬る。

31なぜ、人は神に、

『私たちは罪を犯しましたが、もういたしません』

と言わないのだろう。

32あるいは、

『自分がどんな悪いことをしたのかわかりません。

教えていただければ、すぐに改めます』

と言わないのだろう。

33神は、あなたの注文どおりに法を曲げるだろうか。

あなたの移り気に合わせて、

宇宙の秩序を変えるだろうか。

答えはわかりきっている。

34-35ヨブさん、知恵ある人なら、

あなたが思慮のない話し方をしているという

私の意見に同意するはずだ。

36あんなに神を悪く言ったのだから、

厳罰を受けて当然だ。

37あなたは、もろもろの罪に、

背き、傲慢、冒瀆の罪を加えたのだ。」

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 34:1-37

1ኤሊሁ በመቀጠል እንዲህ አለ፤

2“እናንት ጠቢባን፣ ቃሌን ስሙ፤

ዐዋቂዎችም አድምጡኝ።

3ምላስ ምግብን አጣጥሞ እንደሚለይ፣

ጆሮም የንግግርን ለዛ ለይቶ ያውቃል።

4የሚበጀንን እንምረጥ፣

መልካሙንም አብረን እንወቅ።

5“ኢዮብ እንዲህ ይላል፤ ‘እኔ ንጹሕ ነኝ፤

እግዚአብሔር ግን ፍትሕ ነሣኝ፤

6እውነተኛ ብሆንም፣

እንደ ውሸታም ተቈጥሬአለሁ፤

በደል ባይኖርብኝም፣

በማይፈወስ ቍስል ተመትቻለሁ።’

7ፌዝን እንደ ውሃ የሚጠጣት፣

እንደ ኢዮብ ያለ ሰው ማን ነው?

8ከክፉ አድራጊዎች ጋር ይተባበራል፤

ከኀጢአተኞችም ጋር ግንባር ይፈጥራል።

9‘እግዚአብሔርን ለማስደሰት መሞከር፣

ለሰው አንዳች አይጠቅምም’ ብሏልና።

10“ስለዚህ፣ እናንተ አስተዋዮች ስሙኝ፤

ክፋትን ማድረግ ከእግዚአብሔር ዘንድ፣

በደልንም መፈጸም ሁሉን ከሚችል አምላክ ይራቅ።

11ለሰው እንደ ሥራው ይመልስለታል፤

እንደ አካሄዱም ይከፍለዋል።

12በእውነት እግዚአብሔር ክፋትን አይሠራም፤

ሁሉን የሚችል አምላክ ፍትሕን አያጣምምም።

13ምድርን እንዲገዛ የሾመው አለን?

የዓለምስ ሁሉ ባለቤት ያደረገው ማን ነው?

14እርሱ መንፈሱን መልሶ ቢወስድ፣

እስትንፋሱንም ወደ ራሱ ቢሰበስብ፣

15ሥጋ ለባሽ ሁሉ በአንድነት በጠፋ፣

ሰውም ወደ ዐፈር በተመለሰ ነበር።

16“ማስተዋል ካለህ ይህን ስማ፤

እኔ የምለውንም አድምጥ።

17ፍትሕን የሚጠላ ሊያስተዳድር ይችላልን?

አንተስ ጻድቁንና ኀያል የሆነውን ትኰንናለህ?

18ነገሥታትን ‘የማትረቡ ናችሁ፣’

መኳንንትንም፣ ‘ክፉዎች ናችሁ’

የሚላቸው እርሱ አይደለምን?

19ሁሉም የእጁ ሥራ ስለሆኑ፣

እርሱ ለገዦች አያደላም፤

ባለጠጋውንም ከድኻው አብልጦ አይመለከትም።

20እነርሱም እኩለ ሌሊት ላይ በድንገት ይሞታሉ፤

ሕዝብ ተንቀጥቅጦ ሕይወቱ ያልፋል፤

ኀያላኑም የሰው እጅ ሳይነካቸው ይወገዳሉ።

21“ዐይኖቹ የሰውን አካሄድ ይመለከታሉ፤

ርምጃውንም ሁሉ ይከታተላሉ።

22ክፉ አድራጊዎች የሚደበቁበት፣

ጨለማ ስፍራ ወይም የሞት ጥላ የለም።

23ሰው ለፍርድ ፊቱ ይቀርብ ዘንድ፣

እግዚአብሔር ቀጠሮ አይዝለትም።

24ያለ ምንም ጥያቄ ኀያላንን ያንኰታኵታል፤

ሌሎችንም በቦታቸው ይሾማል።

25እርሱ ሥራቸውን ሁሉ ስለሚያውቅ፣

በሌሊት ይገለብጣቸዋል፤

እነርሱም ይደቅቃሉ።

26ስለ ክፋታቸውም፣

በሰው ሁሉ ፊት ይቀጣቸዋል፤

27እርሱን ከመከተል ተመልሰዋልና፤

መንገዱንም ችላ ብለዋል።

28የድኾች ልቅሶ ወደ እርሱ እንዲደርስ ሰበብ ሆኑ፤

የመከረኞችን ጩኸት ሰማ።

29እርሱ ዝም ቢል፣ ማን ሊወቅሰው ይችላል?

ፊቱንስ ቢሰውር፣ ማን ሊያየው ይችላል?

እርሱ ከሰውም፣ ከሕዝብም በላይ ነው፤

30ይህም የሆነው ዐመፀኛው ሕዝቡን እንዳይገዛ፣

ወጥመድም በፊታቸው እንዳይዘረጋ ነው።

31“ሰው ለእግዚአብሔር እንዲህ ቢል የተሻለ ነበር፤

‘እኔ በደለኛ ነኝ፤ ከእንግዲህ ግን አልበድልም፤

32ማየት ያልቻልሁትን አስተምረኝ፤

ኀጢአት ሠርቼ እንደ ሆነም፣ ደግሜ አልሠራም።’

33ታዲያ አንተ ለመናዘዝ ፈቃደኛ ሳትሆን፤

እግዚአብሔር እንደ ወደድህ ይከፍልሃልን?

መወሰን ያለብህ አንተ ነህ እንጂ፣ እኔ አይደለሁም፤

እንግዲህ የምታውቀውን ንገረኝ።

34“አስተዋዮች ይናገራሉ፤

የሚሰሙኝም ጠቢባን እንዲህ ይሉኛል፤

35‘ኢዮብ ያለ ዕውቀት ይናገራል፤

ቃሉም ማስተዋል ይጐድለዋል።’

36ምነው ኢዮብ እስከ መጨረሻ በተፈተነ ኖሮ!

እንደ ክፉ ሰው መልሷልና፤

37በኀጢአቱም ላይ ዐመፅን ጨምሯል፤

በመካከላችን ሆኖ በንቀት አጨብጭቧል፤

በእግዚአብሔርም ላይ ብዙ ተናግሯል።”