התגלות 7 – HHH & NASV

Habrit Hakhadasha/Haderekh

התגלות 7:1-17

1לאחר מכן ראיתי ארבעה מלאכים עומדים בארבע פינות הארץ ועוצרים את משב ארבע רוחות הארץ, כדי שלא תישוב הרוח בים או ביבשה והכול יעמוד דומם. 2ראיתי מלאך אחר עולה מצד מזרח, שם זורחת השמש, ובידו חותם אלוהים חיים. הוא קרא אל ארבעת המלאכים שקיבלו סמכות וכוח לחבל בארץ, בים ובצומח: 3”חכו! אל תחבלו בארץ, בים ובצומח עד שנחתום את עבדי האלוהים על מצחם.“

4שמעתי שמספר החתומים היה 144,000 מכל שבטי ישראל:

512,000 משבט יהודה

12,000 משבט ראובן

12,000 משבט גד

612,000 משבט אשר

12,000 משבט נפתלי

12,000 משבט מנשה

712,000 משבט שמעון

12,000 משבט לוי

12,000 משבט יששכר

812,000 משבט זבולון

12,000 משבט יוסף

12,000 משבט בנימין.

9אחר כך ראיתי אנשים רבים, שלא ניתן למנותם, מכל הארצות, העמים, הגזעים, השבטים והשפות. הם עמדו לפני כיסא־המלכות ולפני השה, לבושים גלימות לבנות ובידיהם כפות תמרים. 10כל ההמון הזה קרא בקול אדיר: ”הישועה לאלוהינו היושב על כיסא־המלכות ולשה!“

11כל המלאכים – אשר עמדו עתה סביב כיסא־המלכות, סביב הזקנים וארבע החיות – נפלו על פניהם לפני הכיסא, השתחוו לאלוהים 12וקראו: ”אמן! כל הכבוד, הברכה, החכמה, התודה, ההדר, הכוח והעוז לאלוהינו לעולם ועד. אמן!“

13אחד מעשרים־וארבעה הזקנים שאל אותי: ”היודע אתה מיהם הלבושים לבן ומאין באו?“

14”אדוני,“ השבתי, ”אתה יודע.“

”אלה הם אנשים שעברו צרות, רדיפות וסבל רב“, הסביר לי הזקן. ”הם רחצו את גלימותיהם והלבינו אותן בדם השה. 15לכן הם נמצאים כאן לפני כיסא אלוהים; הם משרתים את אלוהים במקדשו יומם ולילה, והוא מגן עליהם, 16הם לא ירעבו ולא יצמאו יותר לעולם, ואף השמש והשרב לא יכו אותם. 17כי השה העומד לפני כיסא־המלכות ירעה אותם ויובילם למעיינות מים חיים, ואלוהים ימחה כל דמעה מעיניהם.“

New Amharic Standard Version

ራእይ 7:1-17

መቶ አርባ አራት ሺሑ መታተማቸው

1ከዚህ በኋላ አራት መላእክት በአራቱ የምድር ማእዘኖች ቆመው አየሁ፤ እነርሱም ነፋስ በምድር ወይም በባሕር፣ ወይም በማንኛውም ዛፍ ላይ እንዳይነፍስ አራቱን የምድር ነፋሶች ያዙ። 2ከዚያም የሕያው አምላክ ማኅተም ያለው ሌላ መልአክ ከምሥራቅ ሲመጣ አየሁ፤ እርሱም ምድርንና ባሕርን ለመጕዳት ሥልጣን የተሰጣቸውን አራቱን መላእክት በታላቅ ድምፅ እንዲህ አላቸው፤ 3“በአምላካችን አገልጋዮች ግንባር ላይ ማኅተም እስከምናደርግባቸው ድረስ ምድርን ወይም ባሕርን፣ ወይም ዛፎችን አትጕዱ።” 4የታተሙትንም ቍጥር ሰማሁ፤ እነርሱም ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ መቶ አርባ አራት ሺሕ ነበሩ፤

5ከይሁዳ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከሮቤል ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከጋድ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

6ከአሴር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከንፍታሌም ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከምናሴ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

7ከስምዖን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከሌዊ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከይሳኮር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

8ከዛብሎን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከዮሴፍ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከብንያም ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ ታተሙ።

ነጭ ልብስ የለበሱ እጅግ ብዙ ሕዝብ

9ከዚህም በኋላ አየሁ፤ እነሆ፤ በዙፋኑና በበጉ ፊት ማንም ሊቈጥራቸው የማይችል ከሕዝብ፣ ከነገድ፣ ከወገን፣ ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሕዝብ ቆመው ነበር፤ እነርሱም ነጭ ልብስ ለብሰው፣ የዘንባባ ዝንጣፊ በእጃቸው ይዘው ነበር። 10በታላቅ ድምፅም እንዲህ ብለው ጮኹ፤

“ማዳን በዙፋኑ ላይ የተቀመጠው፣

የአምላካችንና የበጉ ነው።”

11መላእክቱም ሁሉ በዙፋኑና በሽማግሌዎቹ፣ በአራቱም ሕያዋን ፍጡራን ዙሪያ ቆመው ነበር፤ በዙፋኑ ፊት በግንባራቸው ተደፍተው ለእግዚአብሔር ሰገዱ፤ 12እንዲህም ይሉ ነበር፤

“አሜን፤

ውዳሴና ክብር፣

ጥበብ፣ ምስጋናና፣ ሞገስ፣

ኀይልና ብርታትም፣

ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ለአምላካችን ይሁን፤

አሜን።”

13ከዚያም ከሽማግሌዎቹ አንዱ፣ “እነዚህ ነጭ ልብስ የለበሱት እነማን ናቸው? ከወዴትስ መጡ?” አለኝ።

14እኔም፣ “ጌታ ሆይ፤ አንተ ታውቃለህ” አልሁት።

እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፤ ልብሳቸውንም በበጉ ደም ዐጥበው አንጽተዋል። 15ስለዚህ፣

“በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት ሆነው፣

ቀንና ሌሊት በመቅደሱ ያገለግሉታል፤

በዙፋኑም ላይ የተቀመጠው ድንኳኑን

በላያቸው ይዘረጋል፤

16ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም፤

ከዚህም በኋላ አይጠሙም፤

ፀሓይ አይመታቸውም፤

ሐሩሩም ሁሉ አያቃጥላቸውም፤

17ምክንያቱም በዙፋኑ መካከል ያለው

በግ እረኛቸው ይሆናል፤

ወደ ሕይወት ውሃ ምንጭም ይመራቸዋል፤

እግዚአብሔር እንባን ሁሉ ከዐይናቸው ያብሳል።”